ኢትዮጵያ የአፍሪካ ነጻ ንግድ ቀጠናን ትግበራ ለመምራት ብሔራዊ አስተባባሪ ኮሚቴ ማቋቋሟ ተሰማ

Date:

ኢትዮጵያ የአፍሪካ ነጻ ንግድ ቀጠናን ስምምነት ወደ ሙሉ ትግበራ ለማስገባት የሚያስችል ብሔራዊ አስተባባሪ ኮሚቴ ማቋቋሟን አስታዉቃለች።

ይህ ኮሚቴ ከ55 የአፍሪካ አገራት ጋር የ1.4 ቢሊዮን ሕዝብ እና የ3.4 ትሪሊዮን የአሜሪካን ዶላር ጠቅላላ የአገር ውስጥ ምርት (GDP) ያለውን ግዙፍ የአህጉር ገበያ ለመጠቀም የሚያስችለውን እንቅስቃሴ በቅንጅት ይመራል ተብሏል።

በንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር የሚመራው ይህ ኮሚቴ የገንዘብ ሚኒስቴርን፣ የብሔራዊ ባንክን፣ የጉምሩክ ኮሚሽንን፣ የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴርን እንዲሁም የግሉን ዘርፍ ተወካዮችን ጨምሮ ቁልፍ ተቋማትን ያካተተ ሲሆን፣ የትግበራ ሂደቱን ለመቆጣጠር የሚያስችሉ ንኡሳን ኮሚቴዎችንም አቋቁሟል።

የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር እንደገለፀዉ ፤ አገሪቱ ለትግበራ ዝግጅቷ ማጠናቀቂያ ከደረሱት ስራዎች መካከል 97% የሚሆኑት የታሪፍ መስመሮች በሂደት ወደ ዜሮ ታሪፍ እንዲወርዱ ተወስኗል ብሏል። በተጨማሪም የጉምሩክ ኮሚሽን ለኤክስፖርት የሚላኩ ምርቶች የምስክር ወረቀት የመስጠት ስራውን ማጠናቀቁን ለመረዳት ተችሏል።

CapitalNews

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...