ኢንተር ሚላን ለሙኒኩ ፋይናል አልፈ !

Date:

በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ግማሽ ፍፃሜ የመልስ ጨዋታ ኢንተር ሚላን ባርሴሎናን 4ለ3 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችሏል።

የኢንተር ሚላንን የማሸነፊያ ግቦች ማርቲኔዝ ፣ ካልሀኖግሉ ፣ አቼርቢ እና ፍራቴሲ አስቆጥረዋል።

ለባርሴሎና ግቦችን ኤሪክ ጋርሽያ ፣ ዳኒ ኦልሞ እና ራፊንሀ ከመረብ አሳርፈዋል።

ኢንተር ሚላን በድምር ውጤት ባርሴሎናን 7ለ6 በማሸነፍ ለሻምፒየንስ ሊግ ፍፃሜ ማለፋቸውን አረጋግጠዋል።

ኢንተር ሚላን ባለፉት ሶስት አመታት ለሁለተኛ ጊዜ ለአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ፍፃሜ መድረስ ችለዋል።

አሰልጣኝ ሲሞኒ ኢንዛጊ ቡድኑን ከተረከቡ በኃላ ለሁለተኛ ጊዜ ቡድኑን በሻምፒየንስ ሊግ ፍፃሜ አብቅተዋል።

በሙኒክ በሚደረገው የፍፃሜ ጨዋታ ድል የሚቀናቸው ከሆነ አራተኛ የሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫቸውን ማሳካት ይችላሉ።

ከ ኢንተር ሚላን በላይ ብዙ የሻምፒየንስ ሊግ ፍፃሜ ላይ መድረስ የቻለው ክለብ ሪያል ማድሪድ ብቻ ነው።

የሴርያው ክለብ ኢንተር ሚላን የፍፃሜ ጨዋታውን ከፒኤስጂ እና አርሰናል አሸናፊ ጋር ሙኒክ ላይ የሚያደርግ ይሆናል።

ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...

ከ 50 ሚሊዮን በላይ መራጮች በማንዋልና በዲጂታል ተመዝግበዋል

ከየካቲት 28_መጋቢት 28 የመራጮች ምዝገባ ሲካሄድ እንደነበር ይታወቃል። በተለያዩ ጉዳዮች...

በኦሮሚያ ክልል የ4.5 ሚሊዮን ዶላር የአስቸኳይ ጊዜ ድጋፍ ፕሮጀክት ይፋ ተደረገ

ፈያ ኢንተግሬትድ ዴቬሎፕመንት ኦርጋናይዜሽን በኦሮሚያ ክልል የሚከሰቱ የበሽታ ወረርሽኞችን...