ኢንፋንቲኖ የሩሲያን ዕገዳ የማንሳት ሃሳብ አላቸው

Date:

የዓለም አቀፉ እግር ኳስ አስተዳዳሪ አካል (ፊፋ) ፕሬዚዳንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ በሩሲያ ላይ የተጣለውን ዕገዳ ሊያነሱ እንደሚችሉ አስታውቀዋል።

ሩሲያ ከዩክሬን ጋር የገባችውን ጦርነት ተከትሎ ዩክሬንን “ወራለች” በሚል ብሔራዊ ቡድኗም ሆነ የእግር ኳስ ክለቦቿ ከማንኛውም ውድድር ከሦስት ዓመት በፊት መታገዳቸው ይታወሳል።

ኢንፋንቲኖም ይህ ዕገዳ “ያመጣው ለውጥ የለም” በሚል ለማንሳት ማሰባቸውን ይፋ አድርገዋል።

ዕገዳው “ጥላቻ ብቻ” ነው ያመጣው ያሉት ኢንፋንቲኖ እርምጃው ነገሮችን ሊያሻሽላቸው ይችላል የሚል ሃሳብ አላቸው።

የኢንፋንቲኖን አስተያየት ተከትሎ የዩክሬን ስፖርት ሚኒስትር ማትቪ ቢድኒ፥ ኢንፋንቲኖን “ሃላፊነት የጎደላቸው” በማለት ወርፈዋቸዋል።

ሚኒስትሩ “እግር ኳሱን ህፃናት ከሚገደሉበት እውነታ ጋር ሊለያዩት ሞክረዋል” ሲሉ የፕሬዚዳንቱን ሃሳብ ተችተዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...