ከ870 በላይ በሚሆኑ የምግብና ጤና ተቋማት ላይ እርምጃ ተወሰደ

Date:

በአዲስ አበባ ከተማ የህብረተሰቡን ጤና ለመጠበቅ በተከናወነ መጠነ ሰፊ የቁጥጥር ዘመቻ፣ ደንብ በተላለፉ 875 የምግብና ጤና ተቋማት ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ መወሰዱን የአዲስ አበባ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን አስታወቀ።

ባለፉት ሰባት ወራት በማዕከልና በ11ዱም ቅርንጫፎች በተካሄደው በዚህ ኦፕሬሽን፣ 733 ተቋማት የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ የተሰጣቸው ሲሆን፣ 119 ተቋማት ደግሞ በጊዜያዊነት እንዲታሸጉ ተደርጓል።

ከዚህም ባለፈ ከፈቃድ ውጭ ሲሰሩ የተገኙ 3 ተቋማት ፈቃዳቸው እንዲሰረዝ ሲወሰን፣ 20 ተቋማት ደግሞ የገንዘብ ቅጣት ተጥሎባቸዋል።

በቁጥጥሩ ወቅት ጥራት የሌላቸውና ለጤና አስጊ የሆኑ፣ ግምታዊ ዋጋቸው ከ52.6 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጡ የምግብና ጤና ነክ ምርቶች እንዲሁም የትምባሆ ህግን ተላልፈው የተገኙ
ውጤቶች እንዲወገዱ ተደርጓል።

የባለስልጣኑ የምግብና ጤና ነክ ተቋማት ቁጥጥር ዳይሬክተር አቶ እስጢፋኖስ ጌታቸው እንደገለጹት፤ ተቋማት የተቀመጠውን ስታንዳርድ ጠብቀው እንዲሰሩ የክትትልና የድጋፍ ስራው ተጠናክሮ ይቀጥላል።

ይህ እርምጃ በከተማዋ ያለውን የምግብና የመድኃኒት ደህንነት አስተማማኝ ለማድረግ የተከናወነ የቁጥጥር ስራ አካል መሆኑ ተመላክቷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...

የአህጉሪቱን የርስ በርስ ንግድ ልውውጥ 250 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቀደ

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ዋና ፀሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ...