የሀገሪቱ የዋጋ ግሽበት ወደ 9.8 በመቶ ከፍ አለ

Date:

በጥር ወር 2018 ዓ.ም የሀገሪቱ አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት መጠን 9.8 በመቶ መድረሱ ተገለጸ። ይህም ከአንድ ወር በፊት በታህሳስ 2018 ዓ.ም ከነበረው 9.7 በመቶ ጋር ሲነፃፀር መጠነኛ ጭማሪ አሳይቷል።

ይሁን እንጂ የዘንድሮው የጥር ወር የዋጋ ግሽበት መጠን በጥር 2017 ዓ.ም ከነበረው 15.5 በመቶ ጋር ሲነፃፀር ከፍተኛ ቅናሽ የታየበት መሆኑ ተመልክቷል።

ለዋጋ ግሽበቱ መጨመር የምግብና አልኮል ያልሆኑ መጠጦች ዋጋ በ10.4 በመቶ ማደግ ዋነኛ ምክንያት መሆኑ የተጠቀሰ ሲሆን፣ ይህም በዋናነት የአትክልት፣ የስጋ፣ የወተት ተዋፅኦዎች፣ የእንቁላል፣ የፍራፍሬ፣ የዘይትና የስኳር የመሳሰሉት የምግብ ሸቀጦች ዋጋ በመጨመራቸው ነው።

በሌላ በኩል ምግብ ነክ ያልሆኑ የዋጋ ግሽበት 9.0 በመቶ የደረሰ ሲሆን ትራንስፖርት (17.1 በመቶ)፣ ሌሎች እቃዎችና አገልግሎቶች (19.4 በመቶ)፣ ምግብ ቤቶችና ሆቴሎች (12.5 በመቶ)፣ የቤት እቃዎች (11.8 በመቶ) እንዲሁም የአልኮል መጠጦችና ትምባሆ እና ኮሙዩኒኬሽን እያንዳንዳቸው በ10 በመቶ ጭማሪ ተመዝግቦባቸዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...