የሂሳብና ኦዲት ባለሙያዎች ፍቃድ አሰጣጥን ለውጭ ሃገራት ባለሙያዎች ክፍት እንዲያረግ ጥያቄ ቀረበ

Date:

ቦርዱ በሃገር ቤት ያሉ ባለሙያዎችን ብቁ ሳናደርግ ዘርፉን ለውጭ ሃገራት ቢከፈት የውጭ ባለሙያዎች ማራገፊያ መሆንን ያመጣል፤ የአካውንቲንግ ዘርፍን ያቀጭጫል፤ ሃገር ከዘርፉ የምታገኘው ገቢ ተመልሶ ከሃገር እንዲወጣ ምክንያት ይሆናል ሲልም ይሞግታል፡፡

የኢትዮጵያ የሂሳብ አያያዝና ኦዲት ቦርድ በሃገር ቤት ላሉ የሂሳብና ኦዲት ባለሙያዎች የሙያ ፍቃድ ይሰጣል፤በተሰጣቸው ፍቃድ መሰረት ህጉን ተከትለው እየሰሩ መሆኑን እየተቆጣጠረ እርምጃ የሚወስድ መንግስታዊ ተቋም ነው፡፡

በኢትዮጵያ የሂሳብ ስራ በዘፈቀደ ነው የሚሰራው የሚለው ቦርዱ የኢኮኖሚው ዘርፍ በብዙ መንገድ ለውጭ ባለሃብቶች ክፍት በተደረገበትና አንዳንዶቹም ወደ ኢትዮጵያ እየገቡ ባሉበት በዚህ ጊዜ፤ ሙያው የሚጠይቀው ብቃት ያለው ባለሙያ በዚያው ልክ ያስፈልጋል ሲል ዘርፉ የካፒታል ገበያውን ጨምሮ ቢዝነሱ እየጠየቀ ያለው የሂሳብ ባለሙያ በጥቂቱ እንኳን እንደሌለ ተናግሯል፡፡

ቦርዱ ፍቃድ የሰጣቸውን ባለሙያዎች እንዴት ነው እየተቆጣጠረ እርምጃ የሚወስደው ያልናቸው የኢትዮጵያ የሂሳብ አያያዝና ኦዲት ቦርድ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ፍቃዱ አጎናፍር፤ በኦዲተሮች በኩል ያለውን ሲያስረዱ በኢትዮጵያ ሙያዊ ብቃት ያላቸው ኦዲተሮች 230 ናቸው፤3 ዓመታትን የፈጀ ፍተሻ አድርገንባቸዋል፤በተቀመጠው የቦርዱ መስፈርት መሰረት የማይሰሩ ባለሙያዎችን ፍቃድ እስከ ማገድ የደረሰ እርምጃ ስለመውሰዳቸው ጠቅሰዋል፡፡

ፍቃዳቸውን ከመሰረዝ አስቀድሞ ግንዛቤ የመፍጠር ስራን እሰራለሁ የሚለው ቦርዱ በተለይ በቅርቡ ስራ ባስጀመረው የሂሳብ ባለሙያዎች ኢንስቲትዩት በኩል እየተመዘገቡ ፕሮፌሽናል(ሙያዊ ብቃት ያለው) እንሆኑ በማድረግ ላይ መሆኑንም ተጠቁሟል፡፡

በዚህ መንገድ ሰርተን ሙያተኛውን ሙያዊ ብቃት እንዲኖረው ካላደረግን ለትልልቅ ድርጅቶች የሚቀርብ ባለሙያ ጠፍቶ የኬንያ ባለሙያዎች ይህንን ቦታ እየተኩ የመስራታቸው ነገር ቀጥሎ የዘርፉን ውድቀት ያስከትላል ብለውናል አቶ ፍቃዱ፡፡

ሁሉም የኢሳብም ሆነ የኦዲት ባለሙያ ፕሮፌሽናል(ሙያዊ ብቃት ያለው) በኢንስቲትዩቱ ውስጥ ማለፍ አለበት የሚለው ቦርዱ፤የአዲስ አበባ ዩንቨርሲቲን ጨምሮ እነዚህን ስልጠናዎች ወደሚሰጡለት ተቋማት በመሄድ ባለሙያዎች ሙያዊ ብቃታቸውን እንዲያሳድጉ እድሉን ማመቻቸቱንም ቦርዱ ነግሮናል፡፡

በኢትዮጵያ ሙያዊ ብቃት ያላቸውና ቦርዱ የሚያውቃቸው የሂሳብ ባለሙያዎች 500፤ ኦዲተሮች ደግሞ 230 ብቻ ናቸው መባሉን ሰምተናል፡፡

ሸገር 102.1

X :- https://x.com/sheg

Ins

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ጄኤፍኤም 106.7 የሬዲዮ ጣቢያ ለ6 ወራት ታገደ

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ባደረገው የይዘት ክትትልና የኢንስፔክሽን ምልከታ...

ሱልጣን ቢን ኻሊፋ ግሩፕ በኢትዮጵያ በሆቴል ዘርፍ ሊሰማራ ነው

በተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች የኢፌዲሪ ልዩ መልዕክተኛና ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር...

የአሜሪካ የታክስ ህግ የስፔንን የዓለም ዋንጫ ሽልማት ስጋት ላይ ጣለ

የስፔን ብሔራዊ ቡድን ከዓለም ዋንጫ ሊያገኘው ከሚችለው 50 ሚሊዮን...

ህወሓት ከሌሎች ተቃዋሚ ኃይሎች ጋር የሚደረግ ጥምረት አስፈላጊ መሆኑን ገለጸ

ሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ...