የሕዳሴ ግድብን የተመለከተ የሰነድ ማስረጃ ያለው እንዲያቀርብ ተጠየቀ

Date:

የሕዳሴ ግድብን የተመለከተ የምስል፣ የጽሑፍ፣ የቪዲዮና መሰል ሰነዶች ያለው ማንኛውም ግለሰብ፤ ወደ ግድቡ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት የፐብሊክ ዲፕሎማሲ የሕዝብ ግንኙነት ኮምዩኒኬሽን ቢሮ እንዲያቀርብ ተጠይቋል፡፡   

በፕሮጀክቱ የማስተባበሪያ ጽፈት ቤት የፐብሊክ ዲፕሎማሲ የህዝብ ግንኙነት የኮሙኬሽን ኃላፊ አቶ ሰለሞን ዳንኤል ለአሐዱ እንደተናገሩት፤ የሰነድ ማስረጃዎቹ የተፈለጉት የግድቡን ሂደት እና ታሪካዊ ሁነቶችን የሚያሳዩ ማስረጃዎች ለዕይታ ለሚቀረቡበት ሙዚየም እንዲያገለግሉ ነው፡፡

እንደ ግብፅ ያሉ ሀገራት በሕዳሴው ግድብ ላይ የሚያሰራጩትን የሃሰት መረጃ ለመከላከል እንዲህ ዓይነት በማስረጃ ላይ የተመሠረቱ ዶክመንቶችን መሰብሰብ አስፈላጊ መሆኑንም ሥራ አስፈጻሚው ገልጸዋል፡፡

“ሕዳሴው ግድብ በጠላት ፕሮፓጋንዳ የማይቀለበስበት ደረጃ ላይ ደርሷል” ያሉት ኃላፊው፤ የግድቡ ሙሌት ከ98 በመቶ በላይ መድረሱ ተናግረዋል፡፡

(አሐዱ ሬድዮ)

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...