የረመዳን የበጎ አድራጎት ተግባራት በሌሎች ወራትም መቀጠል ይኖርባቸዋል

Date:

ህዝበ ሙስሊሙ በረመዳን ወቅት ሲያከናውናቸው የቆዩትን የበጎ አድራጎት ተግባራት በሌሎች ወራትም መቀጠል እንዳለበት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሼህ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ ተናገሩ። 

ሼህ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ 1 ሺህ 446ኛው ዓመተ ሒጅራ የዒድ አል-ፊጥር በዓልን አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል።

በመግለጫቸውም፥ ለእምነቱ ተከታዮች እንኳን ለ1 ሺህ 446ኛው ዓመተ ሒጅራ የዒድ አል-ፊጥር በዓል አደረሳችሁ በማለት መልዕክት አስተላልፈዋል።

የረመዳን ወር በአንድነት፣ በፍቅር፣ በአብሮነት፣ በመተጋገዝና በመደጋገፍ ማለፉን ተናግረዋል።

ሕዝበ ሙስሊሙ የዒድ አል-ፊጥር በዓልን ሲያከብር በጾም ወቅት ሲያደርገው እንደነበረው እርስ በርስ በመደጋገፍና ለተቸገሩ ወገኖች በማካፈል ሊሆን እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

ሰላም ለሀገር ሁለንተናዊ ዕድገት ወሳኝ መሆኑን ገልፀው፤ እያንዳንዱ ምዕመን ለዘላቂ ሰላም ግንባታ የበኩሉን መወጣት እንዳለበት ማመልከታቸውን ተዘግቧል ።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አትሌት ጉዳፍ ጸጋዬ አዲስ መግለጫ አወጣች

ታዋቂዋ አትሌት ጉዳፍ ጸጋዬ ለስፖርት ወዳጆችና ለደጋፊዎቿ ወቅታዊ መረጃ...

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...