የሮይተርስ የዜና ወኪሎች በኢትዮጵያ ታገዱ

Date:

ኢትዮጵያ የሮይተርስ የዜና ወኪል ጋዜጠኞችን በሀገሪቱ የመሥራት መብት እንደነጠቀች የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ዘገበ።

በመጪው ቅዳሜ እና እሁድ በአዲስ አበባ የሚካሔደውን 39ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ለሮውተርስ የተሰጠው ፈቃድ እንደተሰረዘ የዜና ወኪሉ ቃል አቀባይ በኢሜይል እንደገለጹ ዘገባው ይጠቁማል።

ከዚህ በተጨማሪ መቀመጫቸውን በአዲስ አበባ ያደረጉ ሦስት የሬውተርስ ጋዜጠኞች በኢትዮጵያ የመዘገብ ፈቃድ እንዳልታደሰ ቃል አቀባዩ ገልጸዋል።

ሬውተርስ የውሳኔው ገፊ ምክንያቶች ምን እንደሆኑ ያለው ነገር የለም። ሁሉም ጋዜጠኞች ኢትዮጵያውያን ሲሆኑ ሮውተርስ ስለ ኢትዮጵያ በሚሠራቸው ዘገባዎች የጀርባ አጥንት እንደነበሩ የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ገልጿል።

ሬውተርስ “ጉዳዩን እየገመገመ” እንደሚገኝ እና “ነጻ፣ ገለልተኛ እና አስተማማኝ በሆነ መንገድ” ስለ ኢትዮጵያ ዘገባዎች መሥራቱን እንደሚቀጥል አስታውቋል። የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት በጉዳዩ ላይ ለኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ያቀረበው ጥያቄ ምላሽ እንዳላገኘ በዘገባው ጠቅሷል። የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ባልደረባ ስለ ጉዳዩ መረጃ እንደሌላቸው መናገራቸውን የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ዘግቧል። 

ሬውተርስ ከጥቂት ቀናት በፊት ለሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች ታጣቂዎች በኢትዮጵያ ቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል ማሰልጠኛ መከፈቱን የሚዘግብ ሰፊ ሪፖርት አቅርቦ ነበር ሲል ዶቼቬሌ ዘግቧል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ጥቃት አድራሹ ከካሊፎርኒያ መሆኑን ትራፕ ገለፁ

ትናንት ቅዳሜ ምሽት በዋይት ሃውስ የጋዜጠኞች ማኅበር የእራት ግብዣ...

በኬንያ የመንገደኞች አውሮፕላን ከመስመሩ ወጥቶ ተከሰከሰ

ዛሬ ረፋድ ላይ በኬንያ ማንዴራ የአውሮፕላን ማረፊያ አንድ...

አቶ ጀማል አህመድ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ተጨማሪ 26 ሚሊየን ብር ሰጡ

አቶ ጀማል አህመድ ባሳለፍነው ወር ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ  ከሰጠው...

“የቻይና-አፍሪካ የምርምር ማዕከል”በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሊከፈት ነው

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከቻይና-አፍሪካ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር "የቻይና-አፍሪካ የምርምር...