የቃሊቲ ወደብና ተርሚናል ግንባታ በ510 ሚሊየን ብር ሊካሄድ ነው

Date:

የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ከ510 ሚሊየን ብር በሚልቅ ወጪ የቃሊቲ ወደብና ተርሚናልን ደረጃውን በጠበቀ መልኩ ለመገንባት የሚያስችል ስምምነት ከኢትዮጵያ ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን ጋር ተፈራርሟል።

የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ዋና ሥራ አስፈፃሚ በሪሶ አመሎ (ዶ/ር) እንደተናገሩት የቃሊቲ ወደብና ተርሚናል ለአገልግሎት ሰጪዎችም ሆነ ለተጠቃሚዎች ምቹ አይደለም። በመሆኑም በስምምነቱ መሰረት ፕሮጀክቱ በወቅቱ እንዲጠናቀቅና ምቹ የስራ አካባቢ ለመፍጠር እንደሚሰሩ ገልጸዋል።

የቃሊቲ ወደብና ተርሚናልን የግቢ ውስጥ መንገድ እና የኮንቴይነር ተርሚናል ለማሻሻል ከ510 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት የተመደበ ሲሆን፣ ግንባታው በስድስት ወራት ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሏል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት በዛሬ ዕትሟ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ነሔሴ 16 2018 ዓ.ም ገበያ...

ቱርክ ቤንያሚን ኔታንያሁ ላይ የእስር ማዘዣ አወጣች

ቱርክ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ላይ ዓለም አቀፍ...

በመቀለ የሚካሄደው የአሸንዳ በዓል የመክፈቻ ሥነ ሥርዓት ተሰረዘ

በትግራይ በርካታ ታዳሚ በሚገኝበት በየዓመቱ የሚከበረው የአሸንዳ ባህላዊ በዓል...

የኢትዮጵያ ፖስታ 3 ሺሕ የሚጠጉ ቅርንጫፎቹን ወደ ባንክ ኤጀንትነት ለመቀየር እንቅስቃሴ ጀመረ

የኢትዮጵያ ፖስታ በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ 3 ሺሕ በሚጠጉ ቅርንጫፎቹ...