የባንኮች ውህደት ለግል ባንኮች በርካታ ጥቅሞችን ይዞ ይመጣል

Date:

የባንኮች ውህደት ለግል ባንኮች በርካታ ጥቅሞችን ይዞ ይመጣል ሲሉ የምጣኔ ሀብት ባለሙያው አቶ ዘመዴነህ ንጋቱ ገለጹ፡፡

የባንኮች ውህደት በዋናነት የባንኮቹን የፋይናንስ አቅም ለመሳደግ እንደሚረዳ አቶ ዘመዴነህ ከኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ጋር በነበራቸው ቆይታ ተናግረዋል፡፡

የባንኮች ውህደት ሀሳቡ ሲታሰብ ቆየት ማለቱን ያነሱት ባለሙያው፤ የግል ባንኮች በኢትዮጵያ እንዲሰሩ የተፈቀደበት ሁኔታ የ30 አመት ታሪክ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡

ይህም ከ30 በላይ ባንኮች እንዲቋቋሙ ምክንያት መሆኑን ነው ያነሱት፡፡

አንዳንድ የግል ባንኮች የፋይናስ አቅማቸው ዝቅተኛ መሆኑ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ለመደገፍ አቅም እንዲያንሳቸው ማድረጉን ጠቅሰዋል፡፡

በአፍሪካ ትልልቅ ባንኮች ዝርዝር ውስጥ 3 የሀገር ውስጥ ባንኮች መገኘታቸውን አንስተው፤ ነገር ግን ደረጃቸው ዝቅ ያለ መሆኑን አመላክተዋል፡፡

ትላልቅ የውጭ ባንኮች ወደ ሀገር ውስጥ መግባት እንዳለባቸውና የባንኮች ውህደት ለባንኮች እንደሚያስፈልግም ገልጸዋል፡፡

ባንኮች ሲዋሀዱ በፋይናንስ አቅምም ሆነ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ፣ በአዳዲስ አሰራር እና ኢንቨስተሮችን በመሳብ እንደሚጎለብቱ ተናግረዋል፡፡

ብዙ የግል ባንኮች ስጋት ላይ ቢሆኑም ይህ ውህደት ጥቅሙ ላቅ ያለና ወደፊት ለመቀጠል አስፈላጊ ስለመሆኑም ነው የተናገሩት፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...