የተቃጠለዉ ‎‎ሆስፒታሉ በቀን 700 ታካሚዎች አገልግሎት የሚያገኙበት ነበር

Date:



‎በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የተከሰተው የእሳት አደጋ በሰዎች ጉዳት ባያደርስም በንብረት ላይ ከባድ ጉዳት ማድረሱን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።

‎የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ጉቼ ጉሌ (ዶ/ር)፣ “በርካታ ታካሚዎች የተኙባቸው ክፍሎች ስለነበሩ ሠራተኞች በሙሉ ታካሚ ማውጣት ላይ ትኩረት ስላደረጉ በውስጥ የነበሩ በርካታ ንብረቶች ተቃጥለው ወድመዋል” ሲሉ ተናግረዋል።

‎ሆስፒታሉ በቀን 700 ታካሚዎች አገልግሎት የሚያገኝበት መሆኑን ተገልጿል።‎በመሆኑንም ሆስፒታሉ ወደ ነበረበት እንዲመለስና አገልግሎት እንዲሰጥ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ አጋራ ድርጅቶች አስተዋጽኦ እንዲያደርጉ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ጥሪ አቅርበዋል።

‎ከጤና ሚኒስቴር የተወጣጣ ቡድን ዛሬ ድንገተኛ የእሳት አደጋ ያደረሰውን ጉዳት በቦታዉ በመገኘት የተመለከተ ሲሆን የጤና ሚንስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ፍሬሕይወት አበበ ሆስፒታሉን በአጭር ጊዜ አገልግሎት ለማስጀመር ጤና ሚኒስቴር ከሚመለከታቸዉ ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን አስፈላጊዉን ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል።

‎የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ፣ የወላይታ አስተዳዳሪ፣ የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር፣ የጋሞ ዞን  ‎አና ለሎችም ባለድርሻ አካላት ድጋፍ ድጋፍ እንደሚያደርጉ ገልጸዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ጥቃት አድራሹ ከካሊፎርኒያ መሆኑን ትራፕ ገለፁ

ትናንት ቅዳሜ ምሽት በዋይት ሃውስ የጋዜጠኞች ማኅበር የእራት ግብዣ...

በኬንያ የመንገደኞች አውሮፕላን ከመስመሩ ወጥቶ ተከሰከሰ

ዛሬ ረፋድ ላይ በኬንያ ማንዴራ የአውሮፕላን ማረፊያ አንድ...

አቶ ጀማል አህመድ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ተጨማሪ 26 ሚሊየን ብር ሰጡ

አቶ ጀማል አህመድ ባሳለፍነው ወር ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ  ከሰጠው...

“የቻይና-አፍሪካ የምርምር ማዕከል”በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሊከፈት ነው

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከቻይና-አፍሪካ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር "የቻይና-አፍሪካ የምርምር...