የትራምፕ አስተዳደር የፌደራል የመንግስት ሰራተኞችን ቁጥር ለመቀነስ በሚያደርገው ጥረት፣ ከ1,000 በላይ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ሰራተኞችን ከስራ እንዳሰናበተ የሲቢኤስ ኒውስ ዘገባ አመልክቷል።
ዘገባው እንደሚያመለክተው፣ ባለፈው አርብ ለውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ሰራተኞች በተላከ እና በቢቢሲ የአሜሪካ ዜና አጋር በተገኘ ማስታወቂያ መሰረት፣ በግዳጅ ከስራ ከተሰናበቱት ውስጥ 1,107 የሲቪል ሰርቪስ እና 246 የውጭ አገልግሎት ሰራተኞች ይገኙበታል ተብሏል።
ከዚህ ቀደምም፣ የፌደራል መንግስትን በስፋት የማደራጀት ጥረት አካል በመሆን፣ ከ1,500 በላይ የሚሆኑ ሌሎች የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ሰራተኞች በፈቃደኝነት ስራቸውን ለቀው እንደነበር ተገልጿል።
ይህን የጅምላ ሰራተኛ ቅነሳ የሚተቹ ወገኖች፣ ቅነሳው የመስሪያ ቤቱን ስራ በእጅጉ እንደሚጎዳ ሲከራከሩ ቆይተዋል።
