በጂንካ በተከሰተዉ የማርበርግ ቫይረስ ስርጭት ምክንያት ተጥሎ የነበረዉ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች እንቅስቃሴ ክልከላ መነሳቱን የአሪ ዞን መንግስት ኮሚኒኬሽን ኃላፊ አቶ ደምበላሽ አቦነሀሰ ተናግረዋል።
ለክልከላዉ መነሳት ምክንያት የሆነዉ አሁናዊዉ የማርበርግ ቫይረስ ስርጭት መቀነስና በትራንስፖርት መቋረጥ ምክንያት ማህበረሰቡ የእለት ተዕለት እንቅስቃሴ ላይ ከፍተኛ ጫና እያሳደረ መምጣቱን የዞኑ ግብረሃይል ከገመገመ በኋላ መሆኑን ገልፀዋል።
በመሆኑ ከቀን 27/2018 ዓ.ም ጀምሮ ክልከላው እንዲነሳ መወሰኑን የገለፁት ኃላፊዉ ጉዞዎች ግን ከወትሮዉ በተለየ በጥንቃቄ መሆን እንዳለባቸውና በየመናኻሪያ የሚደረጉ የግንዛቤ ማስጨበጫና የጥንቃቄ ሂደቶች ተጠናክረዉ እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል።
ሕብረተሰቡና የተሽከርካሪ ባለንብረቶችም ይህንኑ በመረዳት አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉም አቶ ደምበላሽ አሳስበዋል።
@tikvahethiopia
