የአበባና ፍራፍሬ እርሻዎች ላይ ከባድ ጉዳት ማድረሱ ተገለጸ

Date:

በኦሮሚያ ክልል ቢሾፍቱ ከተማ በደረሰው ከፍተኛ ንፋስና በረዶ የቀላቀለበት ከባድ ዝናብ፣ በአካባቢው በሚገኙ የአበባና የፍራፍሬ እርሻዎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱ ተገለጸ፡፡

በዚህም ከትናንት በስቲያ ሰኞ ሁለት ዋና ዋና እርሻዎች ላይ የሚገኙት ግሪን ሐውሶች ሙሉ በሙሉ መዉደማቸዉን ካፒታል ዘግቧል፡፡

ከእነዚህ ሁለት እርሻዎች በተጨማሪ፣ ሌሎች ስምንት የሚሆኑ እርሻዎችም ከፍተኛ የሚባል ጉዳት እንደደረሰባቸው ተጠቁሟል ።

በደረሰው አደጋ ምክንያት በአካባቢው የነበረው የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተቋርጦ የነበረ ሲሆን፣ ይህ ደግሞ የእርሻ ስራዎችን ይበልጥ ተፅዕኖ ዉስጥ እንደሚጥለው ተገልጿል።

በአደጋው የተጎዱት አምራቾች፣ በቀጣይ ወራት ዉስጥ ወደ ስራ ካልተመለሱ በባንክ ያለባቸው ብድርና ለመንግሥት የሚከፍሉት ግብር ከፍተኛ ጫና እንደሚያሳድርባቸው መግለጻቸው ተዘግቧል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...