የአዲስ አበባ የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት ከሠአት ይፋ ይሆናል

Date:

የዘንድሮው የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከአምናው የተሻለ ውጤት የተመዘገበበት መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ አስታወቀ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ አጠቃላይ ካውንስል አባላት የ2017 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የማለፊያ ውጤት 50% እንዲሆን ወስነዋል። 

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዘላለም ሙላቱ (ዶ/ር) በከተማ አስተዳደሩ የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት በየዓመቱ መሻሻል እያሳየ መሆኑን ተናግረዋል።

የ2017 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት ዛሬ ከሰአት በኋላ ይፋ ይሆናል ተብሏል።

በቀጣይ ጥቂት ቀናትም የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ውጤት ይፋ ይደረጋል ነው የተባለው።

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በ2017 ዓ.ም 70 ሺህ 525 ተማሪዎች የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስደዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...