የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሥራ አመራር ቦርድ ሐምሌ 22 ቀን 2017 ዓ/ም ባደረገው ስብሰባ ለ14 የዩኒቨርሲቲያችን ምሁራን የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ሰጠ፡፡ በዚህም መሰረት:-
- ዶ/ር ተስፋዬ ከበደ ለገሰ- በቦዲ ኢሜጂንግ
- ዶ/ር መሳይ ሙሉጌታ ተፈራ- በሶሺዮ ኢኮኒሚክ ዴቨሎፕመንት ጥናት
- ዶ/ር ዲንቃ አያና አጋ- በቬተርነሪ ፓራሲቶሎጂ
- ዶ/ር ፉፋ አቡና ኩራ- በቬተርነሪ ፐብሊክ ሄልዝ
- ዶ/ር ወንደሰን ተስፋዬ አብሬ- በሊንጉዊስቲክስ
- ዶ/ር አማኑኤል ገብሩ ወ/አረጋይ- በሚዲያ እና ኮሙኒኬሽን ጥናቶች
- ዶ/ር ሙራዱ አብዶ ሱሩር- በህግ
- ዶ/ር ክሪስቶፍ ቫነደርቤከን- በፐብሊክ ሎዉ
- ዶ/ር እሸቴ ብርሃን አጣናው- በኢንደስትሪያል ኢንጅነሪንግ
- ዶ/ር ዋሴ ከበደ – በሶሻል ወርክ
- ዶ/ር ሰይፈ ተፈሪ ደሌ- በሜዲካል ፊዚክስ ዲያግኖስቲክስ ራዲዮሎጂ
- ዶ/ር ወርቁ መኮንን- በሰዉ ሃብት አስተዳደር
- ዶ/ር ሺፈራዉ ታዬ- በስትራክቸራል ኢንጂነሪንግ
- ዶ/ር ደረጀ ሃይሉ- በዉሃ ሃብት ኢንጂነሪንግ
መስኮች ከላይ ከተጠቀሰው ቀን ጀምሮ ምሁራኑ የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ የተሰጣቸው መሆኑና ይህም ለዩኒቨርስቲው አካዳሚያዊ ቁመና ወሳኝ እርምጃ እንደሆነ በወቅርቱ ተገልጿል፡፡
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የስራ አመራር ቦርድ በኢ.ፌ.ዴ.ሪ የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት ”ስለ ራስገዝ ዩኒቨርሰቲ ለመደንገግ በወጣ” አዋጅ ቁጥር 1294/2015 በተሰጠው ስልጣን መሠረት ነው በዩኒቨርሲቲው ሴኔት የቀረቡለትን የማዕረግ እድገት ያጸደቀው፡፡
