የአፍሪካ ሕብረት እና ዩናይትድ አረብ ኤምሬትስ በሶማሊያ ሉዓላዊነትና በቀጠናዊ ሰላም ላይ በጋራ ለመስራት ተስማሙ

Date:

የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን እና የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ የሶማሊያን ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት ለማክበር እንዲሁም በአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን ያላቸውን ቁርጠኝነት በይፋ አስታውቀዋል።

የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር ማህሙድ አሊ ዩሱፍ እና የኤምሬትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሼክ ሻክቦት ቢን ናህያን አል ናህያን አዲስ አበባ ከተማ ላይ ባደረጉት ምክክር፣ የሁለቱን ወገኖች ስትራቴጂካዊ ትብብር ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ ስምምነት ላይ መድረሳቸውን ለአሐዱ በላኩት ጋዜጣዊ መግለጫ ገልጸዋል።

ውይይቱ በዋናነት ያተኮረው በሶማሊያ መረጋጋት፣ በሱዳን ወቅታዊ ቀውስ እና በአህጉሪቱ በሚታዩ የፖለቲካ አለመረጋጋቶች ዙሪያ ሲሆን፣ ሁለቱም ወገኖች ለአፍሪካ ሰላምና ኢኮኖሚያዊ እድገት በጋራ ለመቆም ቃል ገብተዋል።

በተለይም በሶማሊያ ጉዳይ ላይ ያተኮረው ንግግር የአገሪቱን ደህንነትና የግዛት አንድነት በጽኑ እንደሚደግፉ ያረጋገጠ ሲሆን፣ ይህ አቋም በቀጠናው ያለውን ውጥረት ለማርገብ ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ተመላክቷል።

ይህ የፖለቲካ ምክክር በ2019 የተፈረመውን የመግባቢያ ስምምነት ተከትሎ በ2025 በአቡዳቢ የተጀመረውን የውይይት መድረክ መሠረት ያደረገ መሆኑ ተጠቁሟል።

ከዚህ ጎን ለጎንም በሱዳን ዕየታየ ያለው ቀውስ በአስቸኳይ እንዲቆም፣ ዘላቂ የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲደረግና ለዜጎች ያልተገደበ የሰብዓዊ እርዳታ እንዲቀርብ ጥሪ አቅርበዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...