የአፍሪካ ሕብረት እና ዩናይትድ አረብ ኤምሬትስ በሶማሊያ ሉዓላዊነትና በቀጠናዊ ሰላም ላይ በጋራ ለመስራት ተስማሙ

Date:

የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን እና የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ የሶማሊያን ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት ለማክበር እንዲሁም በአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን ያላቸውን ቁርጠኝነት በይፋ አስታውቀዋል።

የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር ማህሙድ አሊ ዩሱፍ እና የኤምሬትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሼክ ሻክቦት ቢን ናህያን አል ናህያን አዲስ አበባ ከተማ ላይ ባደረጉት ምክክር፣ የሁለቱን ወገኖች ስትራቴጂካዊ ትብብር ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ ስምምነት ላይ መድረሳቸውን ለአሐዱ በላኩት ጋዜጣዊ መግለጫ ገልጸዋል።

ውይይቱ በዋናነት ያተኮረው በሶማሊያ መረጋጋት፣ በሱዳን ወቅታዊ ቀውስ እና በአህጉሪቱ በሚታዩ የፖለቲካ አለመረጋጋቶች ዙሪያ ሲሆን፣ ሁለቱም ወገኖች ለአፍሪካ ሰላምና ኢኮኖሚያዊ እድገት በጋራ ለመቆም ቃል ገብተዋል።

በተለይም በሶማሊያ ጉዳይ ላይ ያተኮረው ንግግር የአገሪቱን ደህንነትና የግዛት አንድነት በጽኑ እንደሚደግፉ ያረጋገጠ ሲሆን፣ ይህ አቋም በቀጠናው ያለውን ውጥረት ለማርገብ ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ተመላክቷል።

ይህ የፖለቲካ ምክክር በ2019 የተፈረመውን የመግባቢያ ስምምነት ተከትሎ በ2025 በአቡዳቢ የተጀመረውን የውይይት መድረክ መሠረት ያደረገ መሆኑ ተጠቁሟል።

ከዚህ ጎን ለጎንም በሱዳን ዕየታየ ያለው ቀውስ በአስቸኳይ እንዲቆም፣ ዘላቂ የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲደረግና ለዜጎች ያልተገደበ የሰብዓዊ እርዳታ እንዲቀርብ ጥሪ አቅርበዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

“ንባብ ለህይወት!” ታላቅ የንባብ ሳምንት እና የመጻሕፍት አውደ ርዕይ

የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት እና የንባብ ለህይወት...

በኢትዮጵያ ከ10 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ከሄፓታይተስ ቢ ቫይረስ ጋር ይኖራሉ

በኢትዮጵያ ከ10 ሚልዮን በላይ ሰዎች ከሄፓታይተስ ቢ እና ከ2...

የቶዮታ ኮሮላ መኪና በኤሌክትሪክ ሊመጣ ነዉ

የዓለማችን ግዙፍ የመኪና አምራች የሆነው ቶዮታ፤ እንደ ቴስላ እና...

ኢራንን ለመምታት የዩናይትድ ስቴትስ ጄቶች ከምድሯ ይነሱ እንደነበር እሥራኤል ይፋ አደረገች

የእሥራኤል መከላከያ ሚንሥትር እሥራኤል ካትስ የዩናይትድ ስቴትስ የጦር ጄቶች...