የእስራኤል ጦር በኢራን ላይ የሚያካሂደው “ዘመቻ ወደ ቀጣይ ምዕራፍ ተሸጋገረ”

Date:

የእስራኤል መከላከያ ሠራዊት፤ በኢራን ላይ የሚካሄደው ዘመቻ ወደ “ቀጣዩ ምዕራፍ እየተሸጋገረ” መሆኑን እና የቴህራን “አገዛዝን እና ወታደራዊ አቅምን ከዚህም የበለጠ የመበታተን” እርምጃውን እንደሚገፋበት ገለጸ።

አሜሪካ እና እስራኤል በሚፈጽሙት ጥቃት ኢራንን “በስትራቴጂካዊ መንገድ እየነጠሉ” መሆኑን የተናገሩት የእስራኤል ጦር ዋና አዛዥ ሌተናንት ጄነራል ኢያል ዛሚር፤ “ከዚህ ቀደም ባይታየ ደረጃ” እያዳከሟት እንደሆነ ጠቅሰዋል።

እስራኤልባለፉት ስድስት ቀናት “ያለ ማቋረጥ” ኢራን ላይ ጥቃት ስትፈጸም መቆየቷን አንስተው፤ “ዘመቻው ባቀድነው ፍጥነት እየሄደ ነው” ብለዋል።

ዋና አዛዡ ባወጡት መግለጫ “የአየር የበላይነትን ያረጋገጥንበትን እና የባለስቲክ ሚሳዔል መሠረታቸውን ያዳከምንበትን ድንገተኛ የጥቃት ምዕራፍ ካጠናቀቅን በኋላ፤ አሁን ወደ ቀጣዩ የዘመቻ ምዕራፍ እየተሸጋገርን ነው” ሲሉ ዕቅዳቸውን አስታውቀዋል።

“በዚህ ምዕራፍ የኢራንን አገዛዝ እና ወታደራዊ አቅሙን የበለጠ እንበታትናለን። አሁን ይፋ የማላደርጋቸው ተጨማሪ ድንገተኛ እርምጃዎች ወደፊት እንወስዳለን” ሲሉም ጽፈዋል።

ወታደራዊ አዛዡ የሊባኖስንም ጉዳይ ባነሱበት በዚህ መግለጫ፤ ሄዝቦላህ ጦርነቱን መቀላቀሉ “ስትራቴጂካዊ ስህተት” እንደሆነ ገልጸዋል። እስራኤል በጦርነት “ግንባርም ሆነ ሊባኖስ ውስጥ በጥልቅ በመግባት በኃይል እያጠቃች” መሆኑን ተናግረዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...