የዛምቤዚን ወንዝ በታንኳ ለማቋረጥ የሞከሩ አሥር ኢትዮጵያውያን ሰመጡ

Date:

15 ኢትዮጵያውያን ሰኞ ምሽት ወንዙን ተሻግረው ወደ ቦትስዋና ለመግባት ሲጠቀሙበት የነበረው ታንኳ መገልበጡን፤ የዛምቢያ ፖሊስ አገልግሎት እና የኢሚግሬሽን መምሪያ በጋራ ባወጡት መግለጫ አስታውቀዋል።

ከአደጋው የተረፉ ሁለት ኢትዮጵያውያን የተገኙ ሲሆን ሦስቱ ግለሰቦች የት እንዳሉ እስካሁን አለመታወቁን የዛምቢያ ሚዲያዎች ዘግበዋል።

የዛምቢያ ባለሥልጣናትየሰለባዎቹ ፍለጋ፣ የተረፉትን ተከታትሎ የማግኘት እና ከአደጋው ጋር የተያያዙ ሁኔታዎችን የማጣራት ሥራ መቀጠሉን ገልጸዋል።

መረጃው እስከወጣበት ጊዜ ድረስ ምንም ዓይነት አስከሬን ባለመገኘቱ የኢትዮጵያውያኑ መስጠም የፍለጋ ውጤቱ እስኪታወቅ በይፋ እንዳልተረጋገጠ የጋራ መግለጫው አክሎ ገልጿል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ጄኤፍኤም 106.7 የሬዲዮ ጣቢያ ለ6 ወራት ታገደ

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ባደረገው የይዘት ክትትልና የኢንስፔክሽን ምልከታ...

ሱልጣን ቢን ኻሊፋ ግሩፕ በኢትዮጵያ በሆቴል ዘርፍ ሊሰማራ ነው

በተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች የኢፌዲሪ ልዩ መልዕክተኛና ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር...

የአሜሪካ የታክስ ህግ የስፔንን የዓለም ዋንጫ ሽልማት ስጋት ላይ ጣለ

የስፔን ብሔራዊ ቡድን ከዓለም ዋንጫ ሊያገኘው ከሚችለው 50 ሚሊዮን...

ህወሓት ከሌሎች ተቃዋሚ ኃይሎች ጋር የሚደረግ ጥምረት አስፈላጊ መሆኑን ገለጸ

ሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ...