የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ ትምህርት ቤት

Date:

ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በአዘዞ ቁጥር 2 መምህራን መኖሪያ ኮንዶሚኒየም መንደር ውስጥ አዲስ የማህበረሰብ ትምህርት ቤት አስገንብቶ አገልግሎት ማስጀመሩን አስታወቀ። ይህ ትምህርት ቤት የዩኒቨርሲቲው መምህራን፣ የሆስፒታል ሐኪሞች፣ የጤና ባለሙያዎችና ሌሎች ሰራተኞች ልጆች ከቅድመ መደበኛ እስከ 12ኛ ክፍል የሚማሩበት ነው።

ፕሮጀክቱ የዩኒቨርሲቲው ሰሞኑን ካስመረቃቸው 22 ኘሮጀክቶች አንዱ ሲሆን፣ የዩኒቨርስቲው ሰራተኞች በአካባቢው ተረጋግተው እንዲቆዩ እና ተጠቃሚ እንዲሆኑ ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር ያለመ ነው።

ትምህርት ቤቱ 10 የቅድመ መደበኛ ክፍሎችን የያዘ ህንፃ እና 28 የመማሪያ ክፍሎች ያሉት ባለ አራት ወለል ህንፃ ያካተተ ሲሆን፣ ደረጃውን የጠበቀ መደበኛ ትምህርት ይሰጣል።

ይህ ተነሳሽነት ለዩኒቨርሲቲው ሰራተኞች ምቹ ሁኔታን ከመፍጠር በተጨማሪ በአካባቢው የትምህርት ጥራትን ለማሻሻል ትልቅ አስተዋፅኦ ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...