ዳማሪዮስ ፋሽን እና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ማሠልጠኛ ከፈተ

Date:

ዳማሪዮስ ፋሽን እና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት በዓለም አቀፍ ደረጃ በፋሽን፣ በስነ ዉበት (ሜካፕ)፣ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ፣ ሴኩሪቲ እና በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ሰልጣኞችን ለማሰልጠን ምዝገባ እንደጀመረ ይፋ አድርጓል።

ዳማሪዮስ ተግባር ተኮር የሆኑ ስልጠናዎች  የሚሰጥ ሲሆን  ከመስከረም ጀምሮ በLevel 2  ዓለም አቀፍ በሆኑ ባለሙያዎች ስልጠናዎች ይሰጣል ተብሏል በተጨማሪም ስልጠናውን ካጠናቀቁ በኋላ በተቋሙ አቅም መሰረት የፋይናንስ አገልግሎቶች እንደሚመቻችላቸው ተገልጿል።

አቅም ለሌላቸው ሰልጣኞች ከዳሽን ባንክ እና ከንብ ባንክ ጋር የዱቤ ብድር አገልግሎት ለመስጠት ስምምነት ተፈፅሟል።

በሜካፕ ትምህርት ክፍል ከMario ሜካፕ ድርጅት ጋር አብሮ ለመስራት ውል መፈፀማቸውን ገልፀው ከቆዳ ስፔሽሊስት ዶክተሮች ጋር በጥምረት አብሮ ለመስራት ውል መፈፀማቸው ተገልጿል።

አሁን ለ20 ቋሚ ሰራተኞች የስራ እድል የተፈጠረ ሲሆን፣ ከRome Business School ጋር ለተማሪዎች የስኮላርሺፕ ስምምነት ተደርጓል።

ተቋሙ ቦሌ ብራስ የሚገኝ ሲሆን በ1200 ካሬ ሜትር ላይ አርፏል፣ 24 ከፍሎች ሲኖሩት፣ ዘጠኝ የመማርያ ከፍሎች፣ አንድ ቤተ መጽሐፍትን ያካተት ተቋም ነው።

ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት በዛሬ ዕትሟ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ነሔሴ 16 2018 ዓ.ም ገበያ...

ቱርክ ቤንያሚን ኔታንያሁ ላይ የእስር ማዘዣ አወጣች

ቱርክ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ላይ ዓለም አቀፍ...

በመቀለ የሚካሄደው የአሸንዳ በዓል የመክፈቻ ሥነ ሥርዓት ተሰረዘ

በትግራይ በርካታ ታዳሚ በሚገኝበት በየዓመቱ የሚከበረው የአሸንዳ ባህላዊ በዓል...

የኢትዮጵያ ፖስታ 3 ሺሕ የሚጠጉ ቅርንጫፎቹን ወደ ባንክ ኤጀንትነት ለመቀየር እንቅስቃሴ ጀመረ

የኢትዮጵያ ፖስታ በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ 3 ሺሕ በሚጠጉ ቅርንጫፎቹ...