ግብፅ ለኤርትራ የመሠረተ ልማት ግንባታ ልታሰማራ ነው

Date:

የግብፅ በኤርትራ ውስጥ ለሚከናወኑ የኢንዱስትሪ እና የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች የሚውሉ የቴክኒክ ባለሙያዎችን ለማሰማራት እና ዝርዝር የአዋጭነት ጥናቶችን ለማካሄድ መዘጋጀቷን አስታወቀች።

ይህ የተነገረው የግብፅ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ካሊድ ሀሺም ከኤርትራ ከፍተኛ የልዑካን ቡድን ጋር በካይሮ ባደረጉት ስብሰባ ወቅት ነዉ።

​ሚኒስትር ካሊድ ሀሺም እንደገለጹት፣ ግብፅ ያላትን የኢንዱስትሪ ልምድ ለኤርትራ በማካፈል በአገሪቱ ስልታዊ የሆኑ ፋብሪካዎች እና የመሠረተ ልማት አውታሮች እንዲገነቡ ድጋፍ ታደርጋለች።

በተጨማሪም ግብፅ በኤርትራ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ማዕከላትን በመገንባት የሰለጠነ የሰው ኃይል ለማፍራት እና በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የንግድ እንቅፋቶች በመቅረፍ ረገድ የበኩሏን ድርሻ ለመወጣት ተስማምታለች።

ይህም በቀይ ባሕር ቀጣና ያለውን ቀጣይነት ያለው የኢኮኖሚ ትስስር ለማጠናከር አዲስ ምዕራፍ እንደሚከፍት ይጠበቃል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...