ጦርነቱ ከተጀመረበት ጊዜ ጀምሮ 1,100 ሕጻናት መቁሰላቸውን ወይም መሞታቸውን ተገለፀ

Date:


በመካከለኛው ምሥራቅ የተከሰተው ጦርነት “በቀጣናው ለሚገኙ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሕፃናት እሰቃቂ ነው” ሲል የተባበሩት መንግሥታት የሕፃናት ኤጀንሲ (ዩኒሴፍ) አስታወቀ።


አሜሪካ እና እስራኤል የካቲት 21/2018 ዓ.ም. ኢራን ላይ ጥቃት ከከፈቱበት ዕለት አንስቶ ከ1,100 በላይ ሕጻናት ጉዳት ወይም ሞት እንደደረሰባቸው ዩኒሴፍ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።


መግለጫው አክሎም ይህ መረጃ በኢራን የተገደሉ 200፣ በሊባኖስ 91፣ በእስራኤል አራት እንዲሁም በኩዌት አንድ ሕፃናትን ያጠቃልላል።
ዩኒሴፍ “የሕፃናትን መገደል እና የአካልጉዳት ማድረስ ወይም ሕጻናት የሚገለገሉባቸውን አስፈላጊ አገልግሎቶች ማውደም እና መቋረጥ ምንም ምከንያት የሚቀርብበት ነገር አይደለም “ ብሏል።


ድርጅቱ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ተዋጊ አካላት “ጦርነቱን ቆሞ ወደ ዲፕሎማሲ ድርድር እንዲመጡ” ያቀረቡትን ጥሪ በድጋሚ እንደሚያቀርብ አስታውቋል።


በተጨማሪም በጦርነት የሚሳተፉ አካላት “በሰላማዊ ሰዎች ላይ የሚደርሰውን ጉዳት ለመቀነስ፣ ይህም ሕፃናትን የሚጎዱ ፈንጂዎችን ከመጠቀም መቆጠብን ጨምሮ፣ የጦር መሳሪያዎችን በመምረጥ ረገድ ሁሉንም አስፈላጊ ጥንቃቄዎች እንዲወስዱ” ጥሪ አቅርቧል።

BBC

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...