ኢትዮጵያ በ2017 በጀት አመት ዘጠኝ ወራት የተለያዩ የእንስሳት ምርቶችን ለውጪ ገበያ ማቅረብ ችላለች ሲል የእንስሳት ልማት ኢንስቲትዮት አስታውቋል።የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አስራት ጤራ ለብስራት ሬዲዮ እንደተናገሩት ኢትዮጵያ ለአለም ገበያ ከምታቀርባቸው የእንስሳት ምርቶች መካከል የለማ እንቁላል ተጠቃሽ ነው።
አያይዘውም በአሁኑ ወቅት ላይ ምርቱን ወደ ተለያዩ የአለም ሀገራት ለሽያጭ እያቀረበች እንደምትገኝ ገልፀዋል።በዚህም መሰረት ባለፋት ዘጠኝ ወራት 235 ቶን የለማ እንቁላል ለውጪ ገበያ እንዲቀርብ መደረጉን ዋና ዳይሬክተሩ ተናግረው በምላሹ 1 ነጥብ 41 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ገቢ መገኘቱን አስረድተዋል ።
የለማ እንቁላል በአሁኑ ወቅት AGP poultry በተባለው ድርጅት አማካኝነት ለውጪ ገበያ እየቀረበ እንደሚገኝ ተገልጿል።ከምርቱ ተቀባይ ሀገራት መካከል ዮጋንዳ ከፍተኛውን ድርሻ መያዟ ሲነገር ኮትዲቯር፣ ሩዋንዳ፣ ኬንያ፣ ጋና እና ማዳጋስካር እንደየቅደም ተከተላቸው የምርቱ ዋንኛ ተቀባይ ሀገራት ናቸዉ፡፡
