ኢትዮጵያ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከለማ እንቁላል ሽያጭ ከ1 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር በላይ ገቢ አገኘች ተባለ

Date:

ኢትዮጵያ በ2017 በጀት አመት ዘጠኝ ወራት የተለያዩ የእንስሳት ምርቶችን ለውጪ ገበያ ማቅረብ ችላለች ሲል የእንስሳት ልማት ኢንስቲትዮት አስታውቋል።የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አስራት ጤራ ለብስራት ሬዲዮ እንደተናገሩት ኢትዮጵያ ለአለም ገበያ ከምታቀርባቸው የእንስሳት ምርቶች መካከል የለማ እንቁላል ተጠቃሽ ነው።

አያይዘውም በአሁኑ ወቅት ላይ ምርቱን  ወደ ተለያዩ የአለም ሀገራት ለሽያጭ እያቀረበች እንደምትገኝ ገልፀዋል።በዚህም መሰረት ባለፋት ዘጠኝ ወራት 235 ቶን የለማ እንቁላል ለውጪ ገበያ እንዲቀርብ መደረጉን ዋና ዳይሬክተሩ ተናግረው በምላሹ  1 ነጥብ 41 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ገቢ መገኘቱን አስረድተዋል ።

የለማ እንቁላል በአሁኑ ወቅት AGP poultry በተባለው ድርጅት አማካኝነት ለውጪ ገበያ እየቀረበ እንደሚገኝ ተገልጿል።ከምርቱ ተቀባይ ሀገራት መካከል ዮጋንዳ ከፍተኛውን ድርሻ መያዟ ሲነገር ኮትዲቯር፣ ሩዋንዳ፣ ኬንያ፣ ጋና እና ማዳጋስካር እንደየቅደም ተከተላቸው የምርቱ ዋንኛ ተቀባይ ሀገራት ናቸዉ፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከባድ ሙስና የተከሰሱትን 4 ተከሳሾችን፤ ፖሊስ ፍርድ ቤት ማቅረብ ሳይችል ቀረ

በከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመስርቶባቸው በፖሊስ የ'ይፈለጋሉ" ማስታወቂያ የወጣባቸው...

ስለመካከለኛው ምስራቅ አዲስ ውጥረት እስካሁን የታወቁ ጉዳዮች

🔸 ትላንት ምሽት ከኢራን ግዛት የተተኮሰ የሮኬት ጥቃት በሰሜናዊ...

የወንጀል ሥነ-ሥርዓትና ማስረጃ ሕጉ በጋዜጣ እስኪታተም ረቂቅ ሰነዶችን ከመጠቀም እንዲቆጠብ የፍትሕ ሚኒስቴር አሳሰበ

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. የፍትሕ ሚኒስቴር አዲሱ የወንጀል ሕግ ሥነ-ሥርዓትና ማስረጃ ሕግ...

ፔንታጎን የእስራኤል ስለላ እንደሚያሳስበው ተገለጸ

ከቅርብ ሳምንታት ወዲህ ፔንታጎን እስራኤል ከፍተኛ ልዑኮችን ጨምሮ የአሜሪካ...