ኢትዮጵያ የብሪክስ ባንክን ለመቀላቀል የተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶችን ድጋፍ ጠየቀች

Date:

ኢትዮጵያ የብሪክስ አዲስ ልማት ባንክ አባል ለመሆን በምታደርገው ጥረት የተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶችን ድጋፍ በይፋ ጠየቀች።

በተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች የኢትዮጵያ አምባሳደር ዑመር ሁሴን በዚሁ ጉዳይ ላይ በቅርቡ በሀገሪቱ የፋይናንስ ሚኒስቴር የዓለም አቀፍ የፋይናንስ ግንኙነት ዳይሬክተርና የባንኩ ተወካይ ከሆኑት ቱራዬያ አልሃሺሚ ጋር ተወያይተዋል።

በውይይታቸው ወቅት አምባሳደር ዑመር ሁሴን ኢትዮጵያ የባንኩ አባል ለመሆን ያላትን ፍላጎትና እየተደረጉ ያሉትን ጥረቶች በዝርዝር ገልጸዋል። በተለይም ኢትዮጵያ ለተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች ያላትን ወዳጅነት በመጥቀስ ለአባልነት ጥያቄያቸው አዎንታዊ ምላሽ እንዲሰጡላቸው ጠይቀዋል። የኢትዮጵያ ኤምባሲም ይህንኑ መረጃ አረጋግጧል።

የተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች ራሷ እ.አ.አ ጥቅምት 4 ቀን 2021 የብሪክስ አዲስ ልማት ባንክን መቀላቀሏ አይዘነጋም።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...