ለቱሪዝም ዘርፍ አስተዋጽኦ ያደረጉ ባለሙያዎች ሊሸለሙ ነው

Date:

ለቱሪዝም ዘርፍ አስተዋጽኦ ያደረጉ ከ30 በላይ የሆቴል እና ቱሪዝም ባለሙያዎችን ሊሸልም እንደሆነ የአዲስ አበባ ሆቴል እና ቱሪዝም ባለሙያዎች ማኅበር አስታወቀ።

የእውቅና እና የሽልማት መርሃግብሩ ነሀሴ 24 ቀን 2017 ዓ.ም በአድዋ ሙዚየም እንደሚከናወን ማህበሩ አስታውቋል።

ተቋሙ ሁለተኛ ዓመቱን በማስመልከት ይህንን ፕሮግራም ያዘጋጀ ሲሆን የሽልማት፣ የምስጋና እና የውይይት መድረኮች በመርሃግብሩ ተካታች እንደሚሆኑ ተጠቁሟል።

ተሸላሚ የሚደረጉት እጩዎች ከየተቋማቱ ተለይተው የሚላኩ እና በሕዝብ ከሚሰበሰብ ድምፅ አሸናፊዎች እንደሚለዩ ተነግሯል።

የህዝብ ድምጽ አሰጣጡ በአንላይን እንደሚድረግም ተገልጿል።

ሆቴሎች አስጎብኚዎች አሰልጣኞች ሼፎች እንዲሁም በአመራር ላይ ያሉ ሴቶች ዲያስፖራዎች እንዲሁም ሌሎች የቱሪዝም ዘርፉ ላይ የሚገኙ እና ቱሪዝምን የሚደግፉ አካላት ተሸላሚ እንደሚደረጉ ተገልጿል።

መርሃ ግብሩ ከሽልማት እና ከምስጋና ባሻገር በኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙ የቱሪዝም ባለድርሻ አካላት መካከል ትብብርን ማጠናከር እና በዘርፉ ያለውን እድገት ለማሳየት አቅም ያለው መሆኑ ተገልጿል።

(ሀገሬ ቴቪ)

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አዲስ ጦርነት ከተቀሰቀሰ ኢራን የበለጠ ምላሽ በመስጠት የተራዘመ ጦርነት እንደምታካሂድ አስታወቀች

ከፍተኛ የኢራን ወታደራዊ ባለሥልጣናት አሜሪካ ሌላ ዙር ጥቃት በአገራቸው...

ምክክሩ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሷል

ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በሥራ ቡድን ደረጃ እየተካሄደ የሚገኘውን...

የጎንደር ቃል-ኪዳን ቤተሰብ 28 የውጭ ዜጋ ተማሪዎችን ከኢትዮጵያውያን ቤተሰቦች ጋር ማስተሳሰሩን ገለጸ

ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በጎንደር ቃል-ኪዳን ቤተሰብ መርሃ-ግብር አማካኝነት በዘንድሮው ዓመት...

የሕግ ተማሪዎቹ አፍሪካን ወክለው ለዓለም አቀፍ የምስለ-ችሎት ፍጻሜ አለፉ

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የህግ ተማሪዎች በአህጉራዊው የዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት...