ለ7ኛው ምርጫ 51 ሺህ ጣቢያዎች መዘጋጀታቸው ተገለጸ

Date:

ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ 51 ሺህ የምርጫ ጣቢያዎች መዘጋጀታቸውን የኢትዮጵያ ሲቪል ማኅበራት ድርጅቶች ጥምረት አስታውቋል።

የምርጫ ታዛቢ ድርጅቶች ጥምረት ዋና ዳይሬክተር አቶ አበራ ኃይለማርያም እንደገለጹት፤ ምርጫውን ለመታዘብ 5 ሺህ ታዛቢዎችን ለማሰማራት የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች ተጠናቀዋል።

ከእነዚህም መካከል 522 የሚሆኑት የረዥም ጊዜ ታዛቢዎች ሲሆኑ፣ የምርጫ ጣቢያዎችን የመጎብኘትና የመራጮች ምዝገባ ሂደቱን የመታዘብ ኃላፊነት ተሰጥቷቸዋል።

ታዛቢዎቹ በወረቀት የሚከናወኑ 12 የመራጮች ምዝገባ ጣቢያዎችን እንዲሁም በታብሌት የሚከናወኑ 8 የምዝገባ ጣቢያዎችን በቅርበት እንደሚከታተሉ ዳይሬክተሩ ገልጸዋል።

የታዛቢዎቹ የክትትል ሥራ እስከ ሚያዝያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም. ድረስ የሚቀጥል ሲሆን፣ በምርጫው ዕለትም ሂደቱን በንቃት እንደሚታዘቡ ታውቋል። ይህም የምርጫውን ተዓማኒነትና ግልጽነት ለማረጋገጥ ዓይነተኛ ሚና ይኖረዋል ተብሏል።

የታዛቢዎችን አቅምና ጥራት ለማረጋገጥ “ዲጂታል ኤሌክሽን ኦብዘርቬሽን ወርክ ስፔስ” የተባለ አዲስ የቴክኖሎጂ ሥርዓት ስራ ላይ መዋሉን አቶ አበራ ጠቁመዋል።

ይህ ቴክኖሎጂ ቀደም ሲል ይስተዋሉ የነበሩ የታዛቢዎች ምልመላና የቁጥጥር ችግሮች ለመፍታት እንዲሁም የጊዜ ብክነትን ለመቀነስ የሚያስችል ነው ተብሏል።

አዲሱ አሠራር በቀጣዩ ጠቅላላ ምርጫ የታዛቢዎችን የሥራ አፈጻጸም በብቃት ለመቆጣጠር እንደሚያስችል ጥምረቱ ገልጿል።

ለአሐዱ ራዲዮ


ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...