ሐማስ ለጋዛ ሰርጥ የቀረበውን አዲስ የተኩስ አቁም ሐሳብ ተቀብያለሁአለ

Date:

የንቅናቄው ኃላፊ ካሊል አል-ሐያ እስራኤል ስምምነቱን እንደማትጥስ ተስፋ እንዳላቸው ገልጸዋል።

የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ቢሮ እስራኤል ከአሜሪካ ጋር በመስማማት በጋዛ የተኩስ አቁም ዙሪያ የራሷን የስምምነት ሐሳብ ለአሸማጋዮቹ ማቅረቧን ቅዳሜ ዕለት አስታውቋል።

እስራኤል ያቀረበችው ምትክ ምክረ ሃሳብ ከአሜሪካ ጋር ስምምነት እንደተደረሰበት ቢገለጽም፣ ምንም ምን ሃሳቦች እንደተካተቱበት የተባለ ነገር የለም።

አሜሪካ በጉዳዩ ላይ በይፋ አስተያየት አልሰጠችም።

እአአ ጥር 19 በሥራ ላይ የዋለው የተኩስ አቁም ስምምነት በዚህ ወር መጀመሪያ ካበቃ በኋላ የእስራኤል ኃይሎች በራፋ በእግረኛ ጦር ዘመቻ ሲጀምሩ፣ በጋዛ ሰርጥ ደግሞ የአየር ድብደባ ማድረጋቸውን ቀጥለዋል።

ሁለቱም ወገኖች የመጀመሪያው የተኩስ አቁም ስምምነት ካበቃ በኋላ ሁለተኛው ዙር ስምምነት ላይ መድረስ ሳይችሉ ቀርተዋል።

ሃማስ በመጀመሪያው የተኩስ አቁም ምዕራፍ 33 ታጋቾችን ለቅቋል።

በኢራን የሚደገፈው ቡድኑ አሁንም 59 እስራኤላውያን በቁጥጥሩ ስር ያሉ ሲሆን ከእነዚህ መካከል ሁሉም በሕይወት ይኖራሉ ተብሎ አይታመንም።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ አደረሳችሁ፤ አደረሰን

ሰማያት ተከፈቱ ፣ ምስጢርም ተገለጠ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዘመዷ ቅድስት...

አባቴ ለእኔ አባት ብቻ አልነበረም፤ ለእናቴ ታማኝ ባል፣ ለሁላችንም ደግሞ የደስታ ምንጭ ነበር

"አባዬ… ዛሬ ላለሁበት ማንነት መሰረት የሆንከኝ አንተ ነህ!" ​የአርቲስት...

የአንበሶቹ ትንሳኤ፦ የዳካር እንባ እና የቴራንጋ ድል

​በዳካር ሰማይ ስር ዛሬ ጨረቃ አልወጣችም፤ ይልቁንም በሚሊዮን የሚቆጠሩ...

የጥምቀት በዓል በመላ ሀገሪቱ በድምቀት እየተከበረ ነው

የጥምቀት በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እና በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት...