ሐማስ ለጋዛ ሰርጥ የቀረበውን አዲስ የተኩስ አቁም ሐሳብ ተቀብያለሁአለ

Date:

የንቅናቄው ኃላፊ ካሊል አል-ሐያ እስራኤል ስምምነቱን እንደማትጥስ ተስፋ እንዳላቸው ገልጸዋል።

የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ቢሮ እስራኤል ከአሜሪካ ጋር በመስማማት በጋዛ የተኩስ አቁም ዙሪያ የራሷን የስምምነት ሐሳብ ለአሸማጋዮቹ ማቅረቧን ቅዳሜ ዕለት አስታውቋል።

እስራኤል ያቀረበችው ምትክ ምክረ ሃሳብ ከአሜሪካ ጋር ስምምነት እንደተደረሰበት ቢገለጽም፣ ምንም ምን ሃሳቦች እንደተካተቱበት የተባለ ነገር የለም።

አሜሪካ በጉዳዩ ላይ በይፋ አስተያየት አልሰጠችም።

እአአ ጥር 19 በሥራ ላይ የዋለው የተኩስ አቁም ስምምነት በዚህ ወር መጀመሪያ ካበቃ በኋላ የእስራኤል ኃይሎች በራፋ በእግረኛ ጦር ዘመቻ ሲጀምሩ፣ በጋዛ ሰርጥ ደግሞ የአየር ድብደባ ማድረጋቸውን ቀጥለዋል።

ሁለቱም ወገኖች የመጀመሪያው የተኩስ አቁም ስምምነት ካበቃ በኋላ ሁለተኛው ዙር ስምምነት ላይ መድረስ ሳይችሉ ቀርተዋል።

ሃማስ በመጀመሪያው የተኩስ አቁም ምዕራፍ 33 ታጋቾችን ለቅቋል።

በኢራን የሚደገፈው ቡድኑ አሁንም 59 እስራኤላውያን በቁጥጥሩ ስር ያሉ ሲሆን ከእነዚህ መካከል ሁሉም በሕይወት ይኖራሉ ተብሎ አይታመንም።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከባድ ሙስና የተከሰሱትን 4 ተከሳሾችን፤ ፖሊስ ፍርድ ቤት ማቅረብ ሳይችል ቀረ

በከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመስርቶባቸው በፖሊስ የ'ይፈለጋሉ" ማስታወቂያ የወጣባቸው...

ስለመካከለኛው ምስራቅ አዲስ ውጥረት እስካሁን የታወቁ ጉዳዮች

🔸 ትላንት ምሽት ከኢራን ግዛት የተተኮሰ የሮኬት ጥቃት በሰሜናዊ...

የወንጀል ሥነ-ሥርዓትና ማስረጃ ሕጉ በጋዜጣ እስኪታተም ረቂቅ ሰነዶችን ከመጠቀም እንዲቆጠብ የፍትሕ ሚኒስቴር አሳሰበ

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. የፍትሕ ሚኒስቴር አዲሱ የወንጀል ሕግ ሥነ-ሥርዓትና ማስረጃ ሕግ...

ፔንታጎን የእስራኤል ስለላ እንደሚያሳስበው ተገለጸ

ከቅርብ ሳምንታት ወዲህ ፔንታጎን እስራኤል ከፍተኛ ልዑኮችን ጨምሮ የአሜሪካ...