ሕወሃት በድጋሚ ሊያገረሽ ይችላል ላለው ቀውስ ዓለማቀፍ ጥሪ አቀረበ

Date:

ሕወሃት በትግራይ ክልል በድጋሚ ሊቀሰቀስ የሚችለውን አስከፊ ጦርነት ለማስቆም ዲፕሎማቶችና አጋር አገራት አፋጣኝ እርምጃ እንዲወስዱ ጥሪ አቀረበ።

ድርጅቱ ለዓለማቀፉ ኅብረተሰብ በጽሁፍ ባስተላለፈው መልዕክት፣ የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት የተፈራረሙትን ሁለቱን ወገኖች ወደ ጠረጴዛ ለማምጣት ንቁ ሚና እንዲጫወቱ የጠየቀ ሲሆን፣ እራሱም ቢሆን ቀውሱን ለመፍታት በሚያስችል ፖለቲካዊ ሂደት ውስጥ ለመሳተፍ ሙሉ በሙሉ ዝግጁ መኾኑን ገልጧል።

ሕወሃት አክሎም፣ ዳግም ጦርነት ሊቀሰቀስ ይችላል የሚለው ስጋት መላ ምት ሳይሆን እውን ለመኾን የተቃረበና ከተከሰተም ቀጠናዊ የመሆን እድሉ ከፍተኛ መሆኑን አስጠንቅቋል።

የመከላከያ ሠራዊት የትግራይን ድንበሮች መክበቡ በሕዝቡ ዘንድ ከባድ ጭንቀት መፍጠሩን የገለጸው ሕወሃት፣ በምዕራብ ትግራይ ያለው “ሕገወጥ” አስተዳደርና በአካባቢው የሚንቀሳቀሱ የታጠቁ የፌደራል መንግሥቱ አጋሮች ከፍተኛ የሰብዓዊ መብቶች ጥሠቶችን መፈጸም መቀጠላቸውንና አዳዲስ መፈናቀሎችም እያጋጠሙ መሆኑን ከስሷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...