ምክር ቤቱ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የሥራ ዘመንን ለ8 ወራት አራዘመ

Date:

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት  ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ፣ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የሥራ ዘመን ለቀጣይ ስምንት ወራት እንዲራዘም በሙሉ ድምፅ አፅድቋል።

የውሳኔ ሃሳቡን ለምክር ቤቱ አባላት ያቀረቡት የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ እውነቱ አለን፤ ኮሚሽኑ እስካሁን ከትግራይ ክልል በስተቀር በአስራ አንድ ክልሎችና በሁለቱ ከተማ መስተዳድሮች አጀንዳ ማሰባሰቡን አስታውቀዋል።

ኮሚሽኑ ለብሔራዊ ጉባኤው ተሳታፊዎችን የመለየት፣ አወያዮችን የመመልመል እና የአጀንዳ ቀረፃ ሥራዎችን እያከናወነ መሆኑን በመጥቀስ፤ በቀጣይ የትግራይ ክልልን በማካተት ሥራውን ማጠናቀቅ እንዲችል ተጨማሪ ስምንት ወራት ቢሰጠው የተሻለ መሆኑን በውሳኔ ሃሳባቸው ጠይቀዋል።

የምክር ቤቱ አባላትም ኮሚሽኑ ቀሪ ሥራዎቹን እንዲያጠናቅቅ በማመላከት የውሳኔ ሃሳቡን ደግፈዋል። በዚህም መሠረት የኮሚሽኑ የቆይታ ጊዜ ከየካቲት 15 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሚቆጠሩ 8 ወራት እንዲራዘም ውሳኔው ጸድቋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...