የሲብክመ ፍትሕ ቢሮ ዐቃቤ ሕግ ስልጣንን አላግባብ በመጠቀም፣የመንግስትን ስራ በማያመች አኳሗን በመምራትና ሀሰተኛ ሰነድ በመስራት፣ ጉቦ በመቀበል ተደራራቢ የሙስና ወንጀል ፈፅመዋል ብሎ የሙስና ወንጀል ክስ እንደመሰረተባቸው እና ፍርድ ቤቱ የጥፋተኝነት ውሳኔ ማስተላለፉን ቀድመን መዘጋባችን ይታወቃል፡፡
በዚህም መሠረት
1ኛ ተከሳሽ ረ/ፕ ጸጋዬ ቱኬ ኪአ የሙስና ወንጀልን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የወጣውን አዋጅ 881/2007 አ.9(2) እና 17 (2) ላይ የተደነገገውን በመተላለፉ በ13 ዓመት ፅኑ እስራትና በ21,000 ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጣ ተወስነል::
2ኛ ተከሳሽ አቶ ተሰማ ዳንጉሼ ወርቦ በ 3 ዓመት ፅኑ እስራትና በ1,000 ብር ተቀጥቶ በ 2 ዓመት ተገድቧል፣
3ኛ አቶ ታሪኩ ታመነ ኦቲሶ በ10 ዓመት ፅኑ እስራትና በ41,000ብር ተቀጥቷል፣
4ኛ ታፈሰ ቱናሻ በ8 ዓመት ፅኑ እስራትና 51,000ብር ተቀጥቷል፣
5ኛ ሰይፉ ደሊሳ በ8 ዓመት ከ6 ወርና በ76,000 ብር ተቀጥቷል::
