የቀድሞው የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ንጋቱ ቂልጡ ቡልቲ በፈጸሙት ከባድ የሙስና ወንጀል የ10 ዓመት ፅኑ እስራት ተበየነባቸው።
የተፈጸመው ወንጀል፦ ስልጣንን ያለአግባብ በመገልገል የራሳቸውን ልጅ ጨምሮ ለተለያዩ ግለሰቦች የመንግስትን መሬት በህገ-ወጥ መንገድ ማስተላለፍ።
የፍርድ ቤቱ ውሳኔ፦ የአሶሳ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የዐቃቤ ህግን ማስረጃዎች መርምሮ ተከሳሹን ጥፋተኛ ብሏቸዋል።
ቅጣቱ፦ 10 (አስር) ዓመት ፅኑ እስራት እና 4,500 ብር የገንዘብ ቅጣት።
ተያያዥ ውሳኔ፦ በህገ-ወጥ መንገድ የተሰጡ የይዞታ ማረጋገጫ ካርታዎች በሙሉ እንዲመክኑና ተወርሰው ለመንግስት ገቢ እንዲሆኑ ታዟል።
