በማርበርግ ቫይረስ የአንድ ሰው ህይወት ሲያልፍ ተጨማሪ ሁለት ሰዎች ቫይረሱ ተገኝባቸዉ

Date:

በዛሬው ዕለት ከተደረጉ 13 የላብራቶሪ ምርመራዎች ተጨማሪ 2 ሰዎች ላይ የማርበርግ ቫይረስ መገኘቱን የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።

በዛሬው ዕለት በተደረገው ምርመራ በቫይረሱ መያዛቸው የተረጋገጠው ታማሚ ከዚህ በፊት ከተገለፀው ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጂንካ ከተማ በለይቶ ማቆያ የነበሩ ሲሆኑ በተመሳሳይ ቦታም የህክምና ክትትላቸውን እያደረጉ እንደሚገኙ ሚኒስቴሩ ገልጿል።

በተጨማሪም በዛሬው ዕለት አንድ ሰው በቫይረሱ ህይወቱ ሲያልፍ በአጠቃላይ በቫይረሱ ህይወታቸው እንዳለፈ የተረጋገጠ ሰዎች ቁጥር አራት መድረሱ ተጠቁሟል።

በሽታው መከሰቱ ከተገለጸበት ቀን አንስቶ እስካሁን 46 የላብራቶሪ ምርመራዎች የተከናወኑ ሲሆን በአጠቃላይ ቫይረሱ በ8 ሰዎች ላይ መገኘቱ ተመላክቷል። እንዲሁም አራት ሰዎች ደግሞ በህክምና ላይ እንደሚገኙ ተጠቁሟል።

የጤና ሚኒስቴር በትናንትናው ዕለት በተደረገ የላብራቶሪ ምርመራ ተጨማሪ 2 ሰዎች በማርበርግ ቫይረስ መያዛቸውን ማስታወቁ አይዘነጋም።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...