ዛሬ ምሽት 12:30 ላይ በታላቁ ኦልድ ትራፎርድ ስታዲየም በሚደረገው የማንቹሪያን ደርቢ ላይ የኳታር የጸጥታ ሀይሎች በደህንነት ስራ ላይ እንደሚሳተፉ ተነገሯል።
የማንቹሪያን ደርቢ ጨዋታ ተጠባቂ ሲሆን ባለሜዳዉ ማንችስተር ዩናይትድ ወደ ወራጅ ቀጠናዉ ዝቅ ላለማለት ለሲቲዝኖቹ ደግሞ የሻምፒዮንስ ሊግ መግቢያ ቦታ ለማግኘት የሚያደርጉት ጨዋታ ይሆናል።
ምንም እንኳ ማንችስተር ዩናይትድ ከታላላቅ ቡድኖች ጋር በሚያደርገዉ ጨዋታ ጠንካ መሆኑን ደጋግሞ ቢያሳይም ከነበረበት የከፍታ ደረጃ ከወረደ ግን አመታት ተቆጥረዋል። ዩናይትድ በማንቹሪያን ደርቢ የበላይነት የያዘዉ ቡድንም ነዉ።
በደርቢዉ ጨዋታ ላይ በማንችስተር ሲቲ በኩል ኤርሊንግ ሃላንድ በጉዳት የማይገኝ ሲሆን ዩናይትድ ማቲያስ ዲሊግትን እንደሚያጣዉ ተዘግቧል።
በጽጥታ ስራዉ ላይ ይሳተፋሉ ለተባሉት የኳታር የጸጥታ ሀይሎችም የማንችስተር ከተማ ፖሊስ ገለጻና መመሪያ ሰጥቷቸዋል።
