በቢል ጌትስ ድጋፍ የሚደረግለት “ታርጌት ማላሪያ” ፕሮጀክት በቡርኪና ፋሶ ታገደ

Date:

የቡርኪና ፋሶ መንግሥት “ታርጌት ማላሪያ” የተባለው ፕሮጀክት በአገር አቀፍ ደረጃ ወዲያውኑ እንዲቋረጥ ማስታወቁን የተለያዩ የቡርኪና ፋሶ የመገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።

በዘር ምህንድስና የተሻሻሉ ትንኞች የነበሩባቸው ሁሉም መኖሪያዎች ታሽገዋል። የተቀመጡት ናሙናዎችም ባዮሎጂካልና የጤና ደህንነትን በሚያረጋግጥ ጥብቅ መመሪያ መሰረት እንደሚወድሙ ተገልጿል።

የቡርኪና ፋሶ ባለሥልጣናት ይህን ውሳኔ ያጸደቁት የሕዝብ ጤናን፣ አካባቢን እና የሀገሪቱን ሳይንሳዊ ሉዓላዊነት ለመጠበቅ አስፈላጊ በመሆኑ ነው ብለዋል።

ይህ እርምጃ ቡርኪና ፋሶ የዘር ምህንድስናን የሚያካትቱ የሳይንስ ፕሮጀክቶችን የምትቆጣጠርበት መንገድ ላይ ትልቅ ለውጥ የሚያመጣ መሆኑን ያሳያል ሲሉም ተናግረዋል።

በአሜሪካዊው ቢሊየነር ቢል ጌትስ የገንዘብ ድጋፍ የሚደረግለት “ታርጌት ማላሪያ” ፕሮጀክት ትንኝን በዘር ምህንድስና በመቀየር የወባ በሽታን ስርጭት ለመቀነስ ያለመ ነበር።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከባድ ሙስና የተከሰሱትን 4 ተከሳሾችን፤ ፖሊስ ፍርድ ቤት ማቅረብ ሳይችል ቀረ

በከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመስርቶባቸው በፖሊስ የ'ይፈለጋሉ" ማስታወቂያ የወጣባቸው...

ስለመካከለኛው ምስራቅ አዲስ ውጥረት እስካሁን የታወቁ ጉዳዮች

🔸 ትላንት ምሽት ከኢራን ግዛት የተተኮሰ የሮኬት ጥቃት በሰሜናዊ...

የወንጀል ሥነ-ሥርዓትና ማስረጃ ሕጉ በጋዜጣ እስኪታተም ረቂቅ ሰነዶችን ከመጠቀም እንዲቆጠብ የፍትሕ ሚኒስቴር አሳሰበ

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. የፍትሕ ሚኒስቴር አዲሱ የወንጀል ሕግ ሥነ-ሥርዓትና ማስረጃ ሕግ...

ፔንታጎን የእስራኤል ስለላ እንደሚያሳስበው ተገለጸ

ከቅርብ ሳምንታት ወዲህ ፔንታጎን እስራኤል ከፍተኛ ልዑኮችን ጨምሮ የአሜሪካ...