በቢል ጌትስ ድጋፍ የሚደረግለት “ታርጌት ማላሪያ” ፕሮጀክት በቡርኪና ፋሶ ታገደ

Date:

የቡርኪና ፋሶ መንግሥት “ታርጌት ማላሪያ” የተባለው ፕሮጀክት በአገር አቀፍ ደረጃ ወዲያውኑ እንዲቋረጥ ማስታወቁን የተለያዩ የቡርኪና ፋሶ የመገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።

በዘር ምህንድስና የተሻሻሉ ትንኞች የነበሩባቸው ሁሉም መኖሪያዎች ታሽገዋል። የተቀመጡት ናሙናዎችም ባዮሎጂካልና የጤና ደህንነትን በሚያረጋግጥ ጥብቅ መመሪያ መሰረት እንደሚወድሙ ተገልጿል።

የቡርኪና ፋሶ ባለሥልጣናት ይህን ውሳኔ ያጸደቁት የሕዝብ ጤናን፣ አካባቢን እና የሀገሪቱን ሳይንሳዊ ሉዓላዊነት ለመጠበቅ አስፈላጊ በመሆኑ ነው ብለዋል።

ይህ እርምጃ ቡርኪና ፋሶ የዘር ምህንድስናን የሚያካትቱ የሳይንስ ፕሮጀክቶችን የምትቆጣጠርበት መንገድ ላይ ትልቅ ለውጥ የሚያመጣ መሆኑን ያሳያል ሲሉም ተናግረዋል።

በአሜሪካዊው ቢሊየነር ቢል ጌትስ የገንዘብ ድጋፍ የሚደረግለት “ታርጌት ማላሪያ” ፕሮጀክት ትንኝን በዘር ምህንድስና በመቀየር የወባ በሽታን ስርጭት ለመቀነስ ያለመ ነበር።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኮሪያ ዘማቾች ያስመዘገቡት አኩሪ ታሪክ በዓለም ሲታወስ ይኖራል

75ኛ ዓመት የኮሪያ ዘማቾች መታሰቢያ በዓል አዲስ አበባ በሚገኘው...

አሜሪካ በጣለችው የባህር ላይ እገዳ ሳቢያ ኢራን 4.8 ቢሊዮን ዶላር አጣች

በአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትዕዛዝ በኦማን ባህረ ሰላጤ ላይ...

ኢሕአፓ ሊያካሂድ የነበረውን ሰላማዊ ሰልፍ ማራዘሙን አስታወቀ

የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) ሚያዚያ 30 ቀን 2018...

እሁድ መንገዶች ለተሽከርካሪዎች ዝግ ይደረጋሉ

መነሻውንና መድረሻውን መስቀል አደባባይ የሚያደረገው ዓለም አቀፉ የዛይድ የበጎ...