በቤተክርስቲያን ሥርዓተ እምነት ላይ የወንጀል ድርጊት በመፈጸም የተጠረጠሩት  በሕግ ቁጥጥር ሥር ውለዋል

Date:

ራሳቸውን ‹‹መሪጌታ›› ጽጌ ስጦታው እና ‹‹መሪጌታ›› ምስጢረ መዝገቡ ብለው የሚጠሩ ግለሰቦች በቅድስት ቤተክርስቲያኛችን ሥርዓተ እምነት ላይ በወንጀል የሚያስጠይቅ ድርጊት ፈጽመዋል  በሚል  ተጠርጥረው የወንጀል አቤቱታ በቀረበባቸው መሠረት የፌደራል ወንጀል ምርመራ ቢሮ በዛሬው ቀን ተጠርጣሪዎችን በሕግ ቁጥጥር ሥር በማዋል የወንጀል ምርመራውን በማጣራት ላይ እንደሚገኝ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን የሕግ ባለሙያዎች ዐቢይ ኮሚቴ አባል ጠበቃ አያሌው ቢታኔ በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል።

ጠበቃ አያሌው አያይዘው እንደገለጹት ከግለሰቦቹ በተጨማሪ  እንዳልካቸው ዘነበ  የተባለ ግለሰብ  በተመሳሳይ ከዚህ ቀደም በቤተክርስቲያናችን ላይ  ፈጽሞታል ተብሎ በተጠረጠረበት ስም ማጥፋት በቅርቡ  በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ውሎ  ቃሉን  ሰጥቶ   በዋስትና መለቀቁን እና በዐቃቤ ሕግ በኩልም የወንጀል አቤቱታ ክስ ቀርቦ በሒደት ላይ  እንደሚገኝ አያይዘው ገልጸዋል። 

የሕግ ባለሙያዎች ዐቢይ ኮሚቴ አባል ጠበቃ አያሌው ቢታኔ በሰጡት መረጃ  ኮሚቴው  ወደ ፊት ጉዳዩን ተከታትሎ የሚያሳውቅ መሆኑን ገልጸዋል።

©EOTC TV

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫ በሚያካሂድባቸው ቦታዎች ሁሉ እሳተፋለሁ

በዘንድሮው ሀገራዊ ምርጫ እንደሚሳተፍ ያስታወቀው የኢትዮጵያ ዜጎች ለማሕበራዊ ፍትህ...

በሲዳማ ክልል ከ62% በመቶ በላይ የሚታረሰው መሬት በአሲዳማነት የተጎዳ ነዉ

በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ የሚታየው የምርታማነት ማነቆ በዋናነት የመሬት አሲዳማነት...

የኢትዮጵያ እዳ እና ሃብት አስተዳደር ኮርፖሬሽን የሥራ ኃላፊዎች ስብሰባ ሳይገኙ ቀሩ

የመንግስት ልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኢትዮጵያ እዳ እና...

የኢትዮጵያ እና ሕንድ የቆየ ዲፕሎማሲዊ ግንኙነት

የኢትዮጵያ እና ሕንድ የቆየ ዲፕሎማሲዊ ግንኙነት የአፍሪካ-ሕንድ...