በቴክሳስ የጎርፍ መጥለቅለቅ አደጋ የሟቾች ቁጥር ከ100 በላይ ሆኗል

Date:

በአሜሪካዋ ቴክሳስ ግዛት ባሳለፍነው አርብ በተከሰተው ከባድ የጎርፍ አደጋ የማቾች ቁጥር ከ 100 በላይ መድረሱ ተገልጿል ።

በማዕከላዊ ቴክሳስ በተከሰተው  ድንገተኛ  የጎርፍ  አደጋ ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ ሰዎች ደብዛቸው  ጠፍቷል።

የማቾች ፍለጋ እና ነብስ የማዳን ስራዎች ጭቃ በተከመረባቸው የወንዝ ዳርቻዎች ላይ ተጠናክሮ ቢቀጥልም  አደጋው ከተከሰተ ከአራት ቀናት በኋላ በሕይወት የተረፉ ሰዎችን የማግኘት ተስፋ እየደበዘዘ መሆኑ እየተገለጸ ይገኛል።

ማዕከላዊ ቴክሳስን የመታው ድንገተኛ ጎርፍ በኬር ካውንቲ  ከፍተኛ ጉዳት ያስከተለ ሲሆን፣ ቢያንስ 84 ሰዎች መሞታቸው ተረጋግጧል። ከእነዚህ ውስጥ 56ቱ ጎልማሶች ሲሆኑ 28ቱ ደግሞ ህጻናት ናቸው።

የካውንቲ የሸሪፍ ጽህፈት ቤት እንደገለጸው፣ በኬር ካውንቲ ከሞቱት ሰዎች መካከል 22 ጎልማሶች እና 10 ህጻናት እስካሁን ማንነታቸው አልታወቀም።

በቀጣዮቹ ቀናት በግዛቱ ተጨማሪ ከባድ ዝናብ እንደሚጠበቅ የተተነበየ ሲሆን ከ 5ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ የአካባቢው ዜጎችም ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ማሳሰቢያ ተሰጥቷል ።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ዋይት ሀውስ በብሔራዊ የአየር ሁኔታ አገልግሎት (NWS) ላይ የበጀት ቅነሳ የአደጋውን ምላሽ ሊገታ ይችላል የሚለውን አስተያየት ውድቅ አደርጓል።

ዘገባው የቢቢሲ ነው

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በጤና አገልግሎት ማስታወቂያዎች ላይ የሕመምተኞችን ምስክርነት መጠቀም ተከለከለ

የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ባወጣው አዲስ መመሪያ መሠረት በኢትዮጵያ ውስጥ...

ሴቶችን በቤት ውስጥ በማገዝ  መልካም ማህበረሰብ መፍጠር ተጀምሯል

በቤት ውስጥ የሚሠሩ ተግባራትን ተከፋፍሎ በመሥራት ሴቶችና እናቶችን መደገፍ...

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...