የትራፊክ አደጋው በዛሬው ዕለት አመሻሽ አከባቢ መኪናው ፍሬን በመበጠሱ ምክንያት በወረዳው በዴሳ ከተማ ውስጥ በሚገኘው ደደሳ ወንዝ ተገልብጦ የደረሰ መሆኑም ተገልጿል።
በአደጋው እስካሁን የ15 ሰዎች ህይወት ማለፉንና 21 ከባድ ጉዳት እንዲሁም 6 ቀላል ጉዳት መድረሱ ተጠቁሟል።
አደጋው ላይ ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎችም በኦቶና ሆስፒታል ህክምና እየተደረገላቸው መሆኑ ተመላክቷል።
46 ሰዎችን ያሳፈረው መኪናው ከአርባምንጭ ዝጊቲ አቦ ዓመታዊ ንግስ በዓል እየተመለሱ የነበሩ የሻሸመኔ ከተማ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ወጣቶች የያዘው እንደሆነም ከወረዳው ያገኘነው መረጃ አመላክቷል።
