በቻይና የኢትዮጵያ ልዩ ቡና የንግድ እና የባህል ማዕከል በይፋ ተመረቀ

Date:

የኢትዮጵያን የቡና ምርት ለቻይና ገበያ በስፋት ለማስተዋወቅ እና ቀጥተኛ የንግድ ትስስር ለመፍጠር የሚያስችል አዲስ የልዩ ቡና የንግድ ማዕከል በቻይና ሁናን ግዛት፣ በይፋ ተመርቋል።

ይህ የማዕከል ምረቃ የተካሄደው በሁለቱ አገራት መካከል የተካሄደውን የ”ቻይና-ኢትዮጵያ የቡና ኢኮኖሚ እና የንግድ ትብብር ኮንፈረንስ” ተገን በማድረግ ነው።

በአሁኑ ወቅት ቻይና የኢትዮጵያ ቡና በብዛት ከሚላክባቸው አገራት መካከል በ4ኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች። የኢትዮጵያ ቡና እና ሻይ ባለስልጣን ይፋ ባደረገው መረጃ መሰረት፣ ባለፉት አምስት ወራት ብቻ 16,300 ሜትሪክ ቶን ቡና ወደ ቻይና የተላከ ሲሆን፣ ይህም 113 ሚሊዮን ዶላር የሚጠጋ የውጭ ምንዛሬ አስገኝቷል።

የኢትዮጵያ ቡና እና ሻይ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አዱኛ ደበላ እንደገለጹት፣ ይህ ማዕከል የኢትዮጵያን ቡና ለቻይናውያን ሸማቾች በቀጥታ ለማድረስ ትልቅ በር ይከፍታል።

ማዕከሉ የዙዙ ከተማን የድንበር ተሻጋሪ የኤሌክትሮኒክ ንግድ መሠረተ ልማት በመጠቀም፣ የንግድ ስራውን ቀልጣፋ እና ተደራሽ ያደርገዋል።

ከንግድ ልውውጡ በተጨማሪ፣ ማዕከሉ የኢትዮጵያን የቡና ባህል ለቻይናውያን በማስተዋወቅ ዘላቂ ደንበኞችን ለማፍራት እንደሚሰራ ተገልጿል።

በዚሁ የኮንፈረንስ መድረክ ላይ በኢትዮጵያ እና በቻይና ኩባንያዎች መካከል በቡና ግብይት፣ በምርት ልውውጥ እና በታዳሽ ሃይል ዘርፎች ላይ የሚያተኩሩ የሁለትዮሽ የትብብር ስምምነቶች ተፈርመዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ አዲስ አበባ ገቡ

ጠቅላይ ሚኒስትሯ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ጠቅላይ...

የቴሌኮም ኦፕሬተሮች የ5 በመቶ የአደጋ ሥጋት ምላሽ ፈንድ ክፍያን ተግባራዊ ማድረግ ጀመሩ

በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱት ሁለቱም የቴሌኮም ኦፕሬተሮች ማለትም ኢትዮ ቴሌኮም እና...

የአውሮፓ ፓርላማ ፕሬዚዳንት ለኢራን ህዝብ – “እኛ ከእናንተ ጋር ነን”

የአውሮፓ ፓርላማ ፕሬዝዳንት ሮቤርታ ሜትሶላ፥ የኢራን መንግስት በተቃዋሚዎች ላይ...

አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ ውክልና ሊኖራት ይገባል

በተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት አፍሪካ ቋሚ ውክልና...