በአማራ ክልል 308 የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ሊገነቡ ነዉ

Date:

የክልሉ ትምህርት ቢሮ ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር 308 ደረጃቸውን የጠበቁ ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ሊገነባ መሆኑን የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ገልጿል ።

የቢሮዉ ኃላፊ አቶ ጥላሁን ወርቅነህ ለብስራት ሬዲዮ እንደተናገሩት 154ቱ ትምህርት ቤቶች በፌደራል ትምህርት ሚኒስቴር በጀት ድጋፍ የሚገነቡ ሲሆን የተቀሩት 154 ደግሞ በወረዳና ህብረተሰቡ ተሳትፎ የሚገነቡ ናቸዉ ።

እነዚህም 308 ትምህርት ቤቶች በሚቀጥሉት ስድስት ወራት ሁሉም ግንባታቸዉ ተጠናቆ ለ2019 የትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር አገልግሎት እንደሚሰጡ አቶ ጥላሁን ጨምረዉ ለጣቢያችን ተናግረዋል።

አሁን ላይ የተቋራጭ ልየታ ስራ እየተከናወነ መሆኑን የገለፁት ኃላፊዉ  የትምህርት ጥራት ችግርን በዘላቂነት ለመፍታትና ብቁና ተወዳዳሪ ዜጎችን ለመፍጠር ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን ማስፋፋትና ማጠናከር ላይ በትኩረት እየተሰራ ነዉ ብለዋል ።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...

ከ 50 ሚሊዮን በላይ መራጮች በማንዋልና በዲጂታል ተመዝግበዋል

ከየካቲት 28_መጋቢት 28 የመራጮች ምዝገባ ሲካሄድ እንደነበር ይታወቃል። በተለያዩ ጉዳዮች...