በኢትዮጵያ የከብቶች ሳንባ በሽታን ለመዋጋት ምርመራ እና ልየታ

Date:

በጣም ተላላፊ እና አደገኛ የሆነው የባክቴሪያ በሽታ ከብቶችን እና ሌሎች የቤት እንስሳትን ያጠቃል። በኢትዮጵያ ብቻ በግምት 3.8 ሚሊዮን ከብቶችን እንደሚያጠቃ ጥናቶች የሚጠቁሙ ሲሆን በዚህም ሀገሪቱ 2.4 በመቶ ከእንስሳት ወደ ሰው ለሚተላለፍ የሳንባ በሽታ ተጋላጭ ናት።

በሽታውን ለመቆጣጠር የተለመደው አሠራር መርምሮ በበሽታው የተያዙትን ማረድ ቢሆንም ኢትዮጵያ እና ሌሎችም ሀገራት በኢኮኖሚ፣ መሠረተ ልማት፣ ሐይማኖታዊ እና ባሕላዊ ምክንያቶች ይህን ዘዴ አይጠቀሙም።

የበሽታውን ስርጭት ለመከላከል ከብቶችን መርምሮ ባክቴርያው የተገኘባቸውን በመለየት ቀሪዎቹን የመከላከል ዘዴ ውጤታማ እንደሆነ በሰበታ የእንስሳት ጤና ኢንስቲትዩት የእንስሳት ሐኪምና ተመራማሪ ዶ/ር ማቲዮስ ላቀው ገልፀዋል።

መርምሮ በበሽታው የተያዙትን የማረድ ዘዴ ብዙ መሠረተ ልማት ባይጠይቅም መርምሮ ከመለየት በሁለት እጥፍ ወድ እንደሆነ ጥናቱ ማረጋገጡን ባለሙያው ጨምረው ገልፀዋል። ሆኖም እርሻዎች በቲቢ የተያዙትን ካልተያዙት የሚለይ በቂ የለይቶ ማቆያ ቦታ ሊኖራቸው እንደሚገባ ጠቁመዋል።

የዓለም ቲቢ ቀን በየዓመቱ መጋቢት 15 ቀን የሚከበር ሲሆን ቀኑ ቲቢን መከላከልና መቆጣጠር አስፈላጊ እንደሆነ በማጉላት ታስቦ ይውላል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ አደረሳችሁ፤ አደረሰን

ሰማያት ተከፈቱ ፣ ምስጢርም ተገለጠ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዘመዷ ቅድስት...

አባቴ ለእኔ አባት ብቻ አልነበረም፤ ለእናቴ ታማኝ ባል፣ ለሁላችንም ደግሞ የደስታ ምንጭ ነበር

"አባዬ… ዛሬ ላለሁበት ማንነት መሰረት የሆንከኝ አንተ ነህ!" ​የአርቲስት...

የአንበሶቹ ትንሳኤ፦ የዳካር እንባ እና የቴራንጋ ድል

​በዳካር ሰማይ ስር ዛሬ ጨረቃ አልወጣችም፤ ይልቁንም በሚሊዮን የሚቆጠሩ...

የጥምቀት በዓል በመላ ሀገሪቱ በድምቀት እየተከበረ ነው

የጥምቀት በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እና በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት...