በዓለም የቤት ውስጥ ሻምፒዮና የተሳተፈው ኢትዮጵያ ልዑክ አቀባበል ተደረገለት

Date:

በቻይና ናንጂንግ በተካሄደው 20ኛው የዓለም የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ሻምፒዮና የተሳተፈው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ልዑክ ዛሬ ጠዋት አዲስ አበባ ገብቷል።

የልዑካን ቡድኑ አባላት ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የጀግና አቀባበል የተደረገላቸው መሆኑን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኑ መረጃ አመላክቷል።

ለልዑካኑ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴዔታ መኪዩ መሃመድ፣ የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት ዶ/ር አሸብር ወልደጊዮርጊስ፣ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ኮማንደር አትሌት ስለሺ ስህን እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች አቀባበል አድርጎላቸዋል።

ኢትዮጵያ በሻምፒዮናው 2 የወርቅ እና 3 የብር ሜዳሊያዎችን በማግኘት ከዓለም 3ኛ እንዲሁም ከአፍሪካ 1ኛ በመሆን ማጠናቀቋ ይታወቃል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ፑቲን እና ሺ ጂንፒንግ በቻይና ውይይት ያደርጋሉ 

የሩሲያው ፕሬዝዳንት ወደ ቻይና የሚያደርጉትን መጪ ጉብኝት አስመልክቶ የክሬምሊን...

ከምዝገባ ካርድ ባሻገር፦ ለነገው ድምፅ የዛሬው ጥንቃቄ

ግዮን መጽሔት :- የምርጫ ካርድዎን በእጅዎ ይዘዋል? እንኳን ደስ...

በጤና አገልግሎት ማስታወቂያዎች ላይ የሕመምተኞችን ምስክርነት መጠቀም ተከለከለ

የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ባወጣው አዲስ መመሪያ መሠረት በኢትዮጵያ ውስጥ...

ሴቶችን በቤት ውስጥ በማገዝ  መልካም ማህበረሰብ መፍጠር ተጀምሯል

በቤት ውስጥ የሚሠሩ ተግባራትን ተከፋፍሎ በመሥራት ሴቶችና እናቶችን መደገፍ...