በጋምቤላ ክልል ወርቅ አዉጪ ድርጅቶች የነዳጅ እጥረት እንዲፈጠር ምክንያት ሆነዋል ተባለ

Date:

በክልሉ ያለዉ የነዳጅ ግብይት ህግ እና ስርአትን ተከትሎ እየተከወነ አይደለም ተብሏል።

በዚህም በክልሉ ሰዉ ሰራሽ የነዳጅ እጥረት በመከሰቱ በማህበረሰቡ እንቅስቃሴ ላይ እክል መፍጠሩን ከክልሉ ንግድ ቢሮ ሰምተናል።

የጋምቤላ ክልል ንግድ ቢሮ ሀላፊ ወ/ሮ ኛሞች ጊል በክልሉ ያሉ የነዳጅ ማደያዎች ከተለያዩ የወርቅ አዉጪ ድርጅቶች ጋር እየፈፀሙት ያለዉ ህገ ወጥ ግብይት ዋነኛ ችግር ሆኗል ብለዋል።

ማደያዎች ያመጡትን ናፍጣ እና ቤንዚል ከታሪፍ በላይ ከመሸጣቸዉ በተጨማሪ ነዳጅ በድብቅ በጥቁር ገበያዉ እየወጣ መሆኑ ተገልጿል።

ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በክልሉ የማደያ ግንባታዎች መበራከት ተስተዉሏል።

በዚህም ፍቃድ ሰጪ ተቋማት የአስፈላጊነት ግምገማዎችን በማድረግ በህጋዊ ስርአት ብቻ ፍቃድ ሊሰጡ እንደሚገባቸዉ ተጠይቋል።

የክልሉ ንግድ ቢሮ በህገ ወጥ የነዳጅ ችርቻሮ ላይ የተሰማሩ ማደያዎች እና ግለሰቦች ለመቆጣጠር እርምጃዎች እየተወሰዱ መሆኑን ገልጿል።

የነዳጅ እጥረት እንዲፈጠር እያደረጉ ነዉ በተባሉ ማደያዎች በመቆጣጠር የነዳጅ ስርጭቱን  ማስተካከል እንዲቻል እየተሰራ መሆኑም ተገልጿል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...