በጋዛ በተከፈተ ተኩስ ከ30 በላይ ሰዎች መገደላቸው ተሰማ

Date:

በጋዛ እርዳታ እየጠበቁ በነበሩ ተረጂዎችላይ በተከፈተ ተኩስ በጥቂቱ 30 ሰዎች መገደላቸው ተሰማ።

በሐማስ የሚመራው የህዝብ አስተዳደር እንደገለጸው በሰሜናዊ ጋዛ በሚገኘው
ዚኪም ድንበር አቅራቢያ ለእርዳታ በተሰባሰቡ ንጹሃን ላይ የእስራዔልጦር አባላት የተኩስ እሩምታ ከፍተዋል።

በዚህም ከ300 በላይ ሰዎች ሲጎዱ በጥቂቱ 30 ሰዎች ደግሞ ለህልፈት ተዳርገዋል
ነው ያለው።

የእስራዔል ጦር በበኩሉ በስፍራው የእርዳታ እህል የጫነ ተሽከርካሪን በከበቡሰዎች ላይ የማስጠንቀቂያ ተኩስ መክፈቱን ጠቅሶ፥ በተኩሱ ስለደረሰው ጥቃት ግን ምንም የሚያውቀው ነገር እንደሌለ ገልጿል።

በአንጻሩ እስራዔል በስፍራው ስለደረሰው ጉዳት እያጣራሁ ነው ብላለች።

በጋዛ የሚገኘው የአል-ሺፋ ሆስፒታል ዳይሬክተር ሞሃመድ አቡ ሳልሚያ በበኩላቸው እስካሁን የ35 ሰዎች አስከሬን
ተቀብለናል ብለዋል።

ዘግየት ብሎ የወጣ የአሶሺየትድ ፕረስ ዘገባ ደግሞ ሆስፒታሉ 45 ሰዎችእንደተገደሉ መግለጹን አስነብቧል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሴቶችን በቤት ውስጥ በማገዝ  መልካም ማህበረሰብ መፍጠር ተጀምሯል

በቤት ውስጥ የሚሠሩ ተግባራትን ተከፋፍሎ በመሥራት ሴቶችና እናቶችን መደገፍ...

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...