እየተከናወነ ባለው የፋይናንስ ጉባኤ ከተሳታፊዎች በግብር አቤቱታ እና ክርክር ጉዳይ ጥያቄ የቀረበላቸው የገቢዎች ሚኒስትር ወ/ሮ አይናለም ንጉሴ ሲመልሱ ገቢዎች ሚኒስቴርም በታክስ ክርክር የሚሸነፍበት ጊዜ መኖሩን ጠቅሰው።
በተጠናቀቀው በጀት አመት በነበረ የግብር ክርክር ወደ 4 ቢሊየን ብር ለግብር ከፋዩ የተፈረደ መሆኑን ጠቅሰዋል።
በተመሳሳይ በ2017 በጀት አመት ወደ 2 ሺ የሚጠቀሱ ግብር ከፋዮች ከስራ መውጣታቸውን የጠቀሱ ሲሆን በአንፃሩ 13 ሺ የሚሆኑ አዳዲስ ግብር ከፋይ ድርጅቶች ወደ ታክስ ስርአት መግባታቸውን ገልፀዋል።
Source: capitalethiopia
