ባለሃብቱ በላይነህ ክንዴ ለበዓል መዋያ የገንዘብ ድጋፍ አደረጉ

Date:

በላይነህ ክንዴ ግሩፕ ዛሬ ባሰራጨው መረጃ መሠረት፣ “በቡሬ ከተማ የሚገኘው ፊቤላ ኢንዱስትሪያል ስራ ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ ለአካባቢው ማህበረሰብ የሚበጁ ማህበራዊ ሀላፊነቶችን በመወጣት ላይ ይገኛል።”

“ፊቤላ ባለፉት 4 ዓመታት ከ200 በላይ የሚሆኑና በዝቅተኛ ገቢ የሚተዳደሩ ወገኖችን በቋሚነት በየወሩ የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ ላይ እንደሚገኝ” የገለጸው ቢኬጂ ግሩፕ፣ “ፊቤላ በቋሚነት ከሚያደርገው ድጋፍ በተጨማሪ በዓላትን መነሻ በማድረግ በዝቅተኛ ገቢ ለሚተዳደሩ ወገኖችም ድጋፍ ሲያደርግ ቆይቷል። የፊታችን እሁድ የሚከበረውን የፋሲካ በዓል ምክንያት በማድረግ ከ1300 በላይ ለሚሆኑና በቡሬ ከተማ ለሚገኙ ወገኖች ድጋፍ አድርጓል።” ሲል ገልጿል።

በተያያዘ ዜና በላይነህ ክንዴ ፋውንዴሽን በአዲስ አበባ ከተማ በዝቅተኛ ገቢ ለሚተዳደሩ ወገኖችም ድጋፍ ማድረጉን ገልጿል።

ፊቤላ ኢንዱስትሪያል፣ ባለፉት አራትላአመታት በቡሬ ከተማና አካባቢው ከገንዘብ ድጋፍ በተጨማሪ የትምህርት ተቋማትና የውሃ መሠረተ ልማት በመገንባት፣ የጤና መድህን በመክፈል፣ በዝቅተኛ ገቢ ለሚተዳደሩ ወገኖችን ቤት ገንብቶ በማስረከብ ማህበራዊ ኃላፊነቱን በመወጣት ላይ እንደሚገኝ ካሰራጨው መረጃ ላይ ተመልክተናል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...