በድሬዳዋ የእስልምና ኃይማኖት ተከታዮች ከስግደት ለሚመለሱ ክርስቲያን ምዕመናን ማዕድ አጋሩ

Date:

በድሬዳዋ የእስልምና ኃይማኖት ተከታዮች ከስግደት ለሚመለሱ የክርስትና እህት ወንድሞቻቸው ማዕድ አጋሩ።

የስቅለት በዓል ዛሬ ከማለዳው ጀምሮ በድሬዳዋ በሚገኙ የክርስትና ኃይማኖት ተከታዮች ዘንድ በስግደት፣ በዝማሬ፣ በፀሎት እና በንስሃ ሲከበር ውሏል።

የእስልምና ኃይማኖት አባቶችና ተከታዮች በየአብያተ ክርስቲያናቱ ደጃፎች ከስግደት ለሚመለሱ የክርስትና እህት ወንድሞቻቸው ማዕድ በማጋራት አብሮነታቸውን አሳይተዋል።

በማዕድ ማቋደሱ ስነስርዓት ላይ በድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር የተመራና የአስተዳደሩን ካቢኔ አባላት ያካተተው ቡድን ተሳታፊ መሆናቸውም ታውቋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...