ባርኮድ የተካተተበት ደረሰኝ ለማሳተም በ6 ቀናት ማቅረብ እንደሚጠበቅባቸው ተገለፀ

Date:

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ ባርኮድ የተካተተበት ደረሰኝ ለማሳተም እስካሁን በተለያዩ ምክንያቶች ያላቀረቡ ግብር ከፋዮች ጥያቄ የማቅረቢያ ጊዜ ሊጠናቀቅ የቀሩት 6 ቀናት ብቻ መሆኑን ገልጿል፡፡

ቢሮው በአዲስ አበባ ከተማ ባርኮድ የተካተተበት ደረሰኝ ለማሳተም ጥያቄያቸውን በማቅረብ አሳትመው መጠቀም የሚጠበቅባቸው 113 ሺህ 37 የደረጃ “ሀ” ፣ የደረጃ “ለ” እና በፈቃደኛነት ደረሰኝ የሚጠቀሙ የደረጃ “ሐ” ግብር ከፋዮች አሉ ሲልም ገልጿል።

ይሁን እንጂ እስከ አሁን ከ60 በመቶ በላይ የሚሆኑ ግብር ከፋዮች ጥያቄያቸውን ያላቀረቡ መሆናቸውን አመላክቷል።

ስለሆነም ልዩ መለያ ኮድ የተካተተበትን ደረሰኝ ለማሳተም ሁሉም ግብር ከፋይ እስከ የካቲት 30 ቀን 2017 ዓ/ም ድረስ ብቻ ጥያቄውን ማቅረብ እንደሚጠበቅበት ማስታወቁን ከቢሮው ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

የፌዴራል ገቢዎች ሚኒስቴር የክልሎችን እና የሁለቱን የከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ ጥያቄዎችን መነሻ በማድረግ ባርኮድ የተካተተበት ደረሰኝ ለማሳተም ግብር ከፋዩ ጥያቄውን የማቅረቢያ ጊዜን በአንድ ወር በማራዘም የካቲት 30 ቀን 2017 ዓ.ም እንዲጠናቀቅ መወሰኑ የሚታወስ ነው፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...