ንጉሥ አርማህ ቴአትር ከሩብ ምዕተ ዓመት በኋላ ወደ መድረክ ተመለሰ

Date:

ቴአትሩ በዶክተር ተሻለ አሰፋ ተዘጋጅቶ ቀደምትና አዳዲስ ተዋንያንን በመያዝ፣ በድርሰትና በዝግጅት ተሻሽሎ፣ በአዲስ መልክ ከእሑድ ሐምሌ 20 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ለዕይታ ሊበቃ እንደሆነ የቴአትሩ ጸሐፊ መልካሙ ዘርይሁን ገልጿል።

ሥድስት ወራት የልምምድ ጊዜ የፈጀው ይህ ታሪካዊ ቴአትር የተዋንያኑን አቅምና ብቃት በሚገባ መፈተን የቻለ እንደነበርም ሰምተናል።

የዛሬ 25 ዓመት በደራሲ መልካሙ ዘርይሁን ተፅፎ በማንያዘዋል እንደሻው የተዘጋጀው ንጉሥ አርማህ ቴአትር ተስፋዬ ገብረሃና እንደ ልዑል፣ ቅድስት ገ/ስላሴ እንደ ልዕልት በመሆን ተጫውተውታል።

ከ25 ዓመታት በኋላም ቴአትሩ ሲመለስ ሁለቱም ተዋንያን ንጉሥና ንግስት ሆነው እንደሚጫወቱ ከደራሲው ሰምተናል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...